Shop Amazon

Sunday, April 21, 2024

UberCal App

Uber Income Calculator

Uber Income Calculator

Please have the Uber official Annual Tax Summary from your Uber driver App to get an accurate result. Also, calculate the total mileage you drove the year. Remember this is just educational information.

Saturday, April 20, 2024

Test 3 uber

Uber Income Calculator

Uber Income Calculator

Please have the Uber official Annual Tax Summary from your Uber driver App to get an accurate result. Also, calculate the total mileage you drove the year. Remember this is just educational information.

Test # Uber earning per hour

Uber Income Calculator

Uber Income Calculator

test

Uber Income Calculator

Uber Income Calculator

Thursday, April 11, 2024

ስታሎን

 


በዘመኑ፣ ስታሎን በሁሉም ፍቺዎች ውስጥ የሚታገል ተዋናይ ነበር። በአንድ ወቅት, በጣም ተሰበረ, እናም የባለቤቱን ጌጣጌጥ ሰርቆ ሸጠ. ነገሮች በጣም ከመከፋታቸው የተነሳ ቤት አልባ ሆነ። አዎ፣ በኒውዮርክ አውቶቡስ ጣቢያ ለ3 ቀናት ተኝቷል። የቤት ኪራይ መክፈል ወይም ምግብ መግዛት አልተቻለም። ዝቅተኛው ነጥብ ውሻውን በመጠጥ ሱቅ ውስጥ ለማያውቅ ሰው ለመሸጥ ሲሞክር መጣ. ውሻውን ለመመገብ ከአሁን በኋላ ገንዘብ አልነበረውም. በ25 ዶላር ብቻ ነው የሸጠው። እያለቀሰ እንደሄደ ይናገራል።


ከሁለት ሳምንታት በኋላ በመሀመድ አሊ እና በቸክ ዌፕነር መካከል የተደረገ የቦክስ ግጥሚያ አይቷል እና ግጥሚያው የዝነኛውን ፊልም ROCKY ስክሪፕት እንዲጽፍ አነሳስቶታል። ለ 20 ሰዓታት ስክሪፕቱን ጻፈ! ሊሸጥ ሞክሮ ለስክሪፕቱ 125,000 ዶላር ቀረበለት። ግን አንድ ጥያቄ ብቻ ነበረው። በፊልሙ ውስጥ STAR ማድረግ ፈልጎ ነበር። እሱ ራሱ ሮኪ ዋና ተዋናይ መሆን ፈለገ። ስቱዲዮው ግን የለም አለ። እውነተኛ ኮከብ ይፈልጉ ነበር።


እሱ "አስቂኝ እና አስቂኝ የሚመስለው" ብለው ተናግረዋል. ስክሪፕቱን ይዞ ወጣ። ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ስቱዲዮው ለስክሪፕቱ 250,000 ዶላር ሰጠው። እምቢ አለ። እንዲያውም 350,000 ዶላር አቅርበዋል። አሁንም እምቢ አለ። የእሱን ፊልም ፈልገዋል, ግን እሱ አይደለም. የለም አለ። በዛ ፊልም ውስጥ መሆን ነበረበት።


ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ስቱዲዮው ተስማምቶ 35,000 ዶላር ለስክሪፕቱ ሰጠው እና እንዲሰራበት ፈቀደ! የቀረው ታሪክ ነው! ፊልሙ በምርጥ ሥዕል፣ በምርጥ ዳይሬክት እና በምርጥ ፊልም ኤዲቲንግ በታዋቂው የኦስካር ሽልማት አሸንፏል። እሱ ለምርጥ ተዋናይ እንኳን ታጭቷል! ፊልሙ ROCKY በአሜሪካ ብሄራዊ ፊልም መዝገብ ቤት እስከ ዛሬ ከታዩ ምርጥ ፊልሞች አንዱ ሆኖ ቀርቧል!


ከራስህ በቀር የምትችለውን ማንም አያውቅም! ሰዎች እርስዎን እንዴት እንደሚመስሉ ይገመግማሉ። እና ባለህ ነገር። ግን ተዋጉ! በታሪክ ውስጥ ላለዎት ቦታ ይዋጉ። ለክብርህ ታገል። በጭራሽ ተስፋ አትቁረጥ!


ምንም እንኳን ሁሉንም ልብሶችዎን መሸጥ እና ከውሾች ጋር መተኛት ማለት ቢሆንም ፣ ምንም አይደለም! ግን አሁንም በህይወት እስካለህ ድረስ ታሪክህ አላለቀም።


ትግሉን ቀጥል። ህልሞችዎን እና ተስፋዎን በህይወት ያቆዩ። ሂድ ውሰድ!!!


ምንጭ፡ BelowZeroToHero


የተጠናቀረ፡ አነቃቂ ታሪኮች


ፒ.ኤስ. ፊልሙ ከወጣ በኋላ ውሻውን የገዛውን ሰው ተከታትሎ በ10ሺህ ገዛው።

Tuesday, April 9, 2024

የሙሉቀን መለስ ቃለ መጠይቅ

ጋዜጠኛ፡- ሙሉቀን ለቃለ መጠይቃችን ፍቃደኛ ስለ ሆንክልን በቅድሚያ በምሥጋና ልጀምር። 
.
ሙሉቀን መለሠ፡- እኔም ስለግብዣችሁ አመሰግናለሁ። 
.
ጋዜጠኛ፡- እስቲ ከውልደትህ እና እድገትህ በመነሳት ጥያቄዬን ልጀምር፣ የልጅነት ጊዜህ ምን ይመስል ነበር፣ መቼ እና የት ተወለድክ፣ ከዚህ ብንነሳስ? 
.
ሙሉቀን፡- የተወለድኩት ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ተብሎ በሚጠራው አገር ነው። 
.
ጋዜጠኛ፡- ዘመኑ ትዝ ይልሃል? 
.
ሙሉቀን፡- እኔ ስወለድ አላውቅም፣ ወላጆቼ የነገሩኝን ነው የማውቀው፤ በእኔ መታወቂያ ላይ ያለውና እኔም የማውቀው በ1946 ነው፣ ነገር ግን እህቴ ደግሞ ከአባታችን መጽሐፍ ላይ በማስታወሻነት ተፅፎ ተገኘ የምትለኝ 1948 ዓ.ም ነው። የ2 ዓመት ስህተት አለ። ይኼኛው ትክክል ነው ለማለት እቸገራለሁ። የማውቀው ግን 1946 ዓ.ም መሆኑንን ነው። 
.
ጋዜጠኛ፡- እስቲ እያንዳንዱን ጥያቄ ከማንሳት ይልቅ፣ አጠር እያደረክ ከትውልድ እስከ እድገት ያለኸን ሕይወት አውጋን፣ ከወላጆችህ ሥም ጀምርልን። 
.
ሙሉቀን፡- ወላጅ አባቴ ቀሰ ገበዝ ተዓምር ጥሩነህ ይባላል። እናቴ ወ/ሮ እናትነሽ ጌታሁን ናት። 
.
ጋዜጠኛ፡- ለወላጆችህ ብቸኛ ልጅ ነህ ወይስ እህቶች እና ወንድሞች አሉህ? 
.
ሙሉቀን፡- አዎ! ሦስት ወንድሞችና እና አራት እህቶች አሉኝ።
.
ጋዜጠኛ፡- አባትህ የቤተክርስቲያን አገልጋይ ቄስ ገበዝ እንደነበሩ አንስተሃል፣ ለመሆን በልጅነትህ ከቤተክርስቲያን ጋር የነበረህ ቅርበት እንዴት ነበር? 
.
ጋዜጠኛ፡- አባቴ ምንጊዜም ቤተክርስቲያን ይዞኝ በመሄድ እኔም የሱን አርዓያነት እንድከተል ይፈልግ ነበር። ከበሮ አመታት፣ አቋቋም፣ የቤተክህነት ሥርዓትም ያስተምረኝ ነበር።
.
ጋዜጠኛ፡- በአብዛኛው ኢትዮጵያዊ የሚያውቅህ እና የሚያደንቅህ በዜማዎችህ ነው። እስቲ ወደ ሙዚቃ ዓለም እንዴት እንደገባህ እንጀምርና፣ ከሙዚቃው ዓለም ተለይተህ የቆየኽባቸውን ደግሞ እንመልከት። ለመሆኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ሙዚቃ ዓለም እንዴት ገባህ? 
.
ሙሉቀን፡- ከምንም ነገር በላይ የምወዳት እናቴ የ5 ዓመት ልጅ እንዳለሁ ሞተችብኝ። በሕፃንነት ዕድሜ ኃዘኔ በጣም የበረታ ነበር። ቀንም ማታም አለቅሳለሁ። ኑሯችን በጣም ተዛባ። በዚህ ላይ ሽፍታ መጥቶ ንብረታችንን ዘርፎ ቤታችንን አቃጠለብን፤ እኛም ሜዳ ላይ ቀረን። ይኽ በሆነ በዓመቱ አጎቴ ከአዲስ አበባ መጣና እኔን መርጦ አስተምረዋለሁ ብሎ ይዞኝ አዲስ አበባ ገባ። 
.
ጋዜጠኛ፡- እስቲ ዝንባሌህ ወደ ሙዚቃ ያመራው መቼ እንደሆነ በቅድሚያ ንገረን? 
.
ሙሉቀን፡- ከመነሻው ልጀምር ብዬ ነው እሱን እነግርሃለሁ፣ ምን አስቸኮለህ? 
.
ጋዜጠኛ፡- መቸኮሌ ሳይሆን ጥያቄውና መልሱ እንዲጣጣም ብዬ ነው። 
.
ሙሉቀን፡- እኔ ለመጀመሪያ ጊዜ የሙዚቃ ፍቅር ያደረብኝ ሠርግ ቤት ሲዘፍኑ ሰውነቴን ሁሉ ይወርረኝ ነበር። እኔም ከዘፈን ጋር የተያያዘ ተፈጠሮ እንዳለኝ ይሰማኝ የነበረው የዛን ጊዜ ነው። 
.
ጋዜጠኛ፡- በል አሁን ወደኋላ ተመልሰህ ቅድም የጀመርከውን ጨርስልኝ 
.
ሙሉቀን፡- የቱን? 
.
ጋዜጠኛ፡- ቅድም አቋርጠኸኝ “ልነግርህ ነው አትቸኩል” ያልከኝን ነዋ! 
.
ሙሉቀን፡- ቅድሙን ብታስጨርስኝ ምን ነበረበት? 
.
ጋዜጠኛ፡- ይቅርታ አሁን መቀጠል ትችላለህ። 
.
ሙሉቀን፡- እሺ ይባርክህ! እናቴ ስትሞትብኝ የእኔ ኃዘን መሪር ነበር። አንድ ቀን በሠፈራችን ውስጥ በጣም አዝኜና ልቤ ተሰብሮ ወዲያ ወዲህ ስል ከሠማይ እጅ ሲመጣ አየሁ ይኼ እጅ በግራ ጡቴ በኩል አንድ ነገር ከውስጤ ወስዶ ሌላ ነገር በመተካት ወደ ሠማይ መልሶ ሲያርግ ተሰማኝ። እኔ አላወቅሁትም እንጂ ገና በሕፃንነቴ ነበር ጌታ መንፈሣዊ ያረገኝ ለካስ፤ አሮጌው ልቤን ወስዶ አዲስ ልብ ነው የተካልኝ።
.
ጋዜጠኛ፡- አንተ ገና ብዙ ያልተጠቀምክበት ትኩስ የህፃን ልጅ አዲስ ልብ ነው ያለህ እንዴት አሮጌ ልብ አልከው? 
.
ሙሉቀን፡- አልተግባባንም መንፈሣዊ እና አለማዊ ልብ ይለያያል። ያንን መንፈሣዊ አዲስ ልብ ነበር ጌታ የተካልኝ። በወቅቱ ግን ሕፃን በመሆኔ አልገባኝም ነበር። 
.
ጋዜጠኛ፡- ከአጎትህ ጋር ወደ አዲስ አበባ ከመጣህ በኋላ ያለውን ሕይወትህን እስቲ አጫውተን? 
.
ሙሉቀን፡- አጎቴ የመጀመሪያውን የት/ቤት ደብተሬን ገዝቶ በላዩ ላይ ‹‹ሙሉቀን መለሰ›› ብሎ የፃፈበት እሱ ነበር። እንግዲህ ከዚያን ቀን ጀምሮ ሙሉቀን ታምር ጥሩነህ መባሌ ቀርቶ ሙሉቀን መለሰ ገሠሠ ሆንኩ። የምንኖርበት ሠፈር ኮልፌ ልዩ ስሙ ፍሪዶሮ የሚባል የልጆች ት/ቤት ነበር። አጎቴ እዛ እንዳስገባኝ ትምህርት በጣም ያስጠላኝ ነበር። በተለይ ሂሳብ የሚባል ትምህርት ጠላቴ ነው። እኔ የምወደው የመዝሙር ክፍለ ጊዜ ሲሆን። ስነ-ፅሁፍም እወድ ነበር። ታዲያ በመዝሙር ክፍለ ጊዜ ስዘምር የተመለከቱኝ አስተማሪ ባንዲራ ሲወጣ እና ሲወርድ የትምህርት ቤቱ ዘማሪ አደረጉኝ።
.
ጋዜጠኛ፡- ለመሆኑ እስከ ስንተኛ ክፍል ተምረሃል? 
.
ሙሉቀን፡- ረሳሁት እስከ ሦስተኛ ክፍል የተማርኩ ይመስለኛል። 
.
ጋዜጠኛ፡- ድምፃዊው ጥላሁን ገሠሠ በሁለት ክፍል ይበልጥሃላ!
.
ሙሉቀን፡- እሱ እዚያ ደርሷል እንዴ? 
.
ጋዜጠኛ:- እኛ የምናውቀው እስከ አምስተኛ ክፍል ድረስ መማሩን ነው። እሱም እንዳንተ ትምሀርት በተለይ ሂሳብ እንደማይወድ ይናገር ነበር። 
.
ሙሉቀን፡- እንዲያውም አሁን ትዝ አለኝ። እኔም አምስተኛ ክፍል ድረስ ነው እዚያ የተማርኩት። 
.
ጋዜጠኛ፡- ጥሩ ድምፅ ያላችሁ ታዋቂ ድምፃዊያን ከአምስተኛ ክፍል በላይ አትሄዱም ማለት ይሆን? 
.
ሙሉቀን፡- እንደ እሱ እንኳን አይመስለኝም፤ አጋጣሚ ሆኖ እንጂ። ብዙ ድምፃዊያን ከዛ በላይ የተማሩና ከዚያም በታች ተምረው ታዋቂ የሆኑ አሉ። 
.
ጋዜጠኛ፡- ከዚያ በኋላ እንዴት ወደምትታወቅበት የሙዚቃ ዓለም ገባህ? 
.
ሙሉቀን፡- አሁንም አትቸኩልብኛ፣ አብራርቼ ልንገርህ።
.
ጋዜጠኛ፡- ይቅርታ እንደሚመችህ ቀጥል።
.
ሙሉቀን፡- አጎቴ ወ/ሮ ፈሰሱ የምትባል ሚስት ነበረችው። በጣም ጠንቋይ ትወዳለች። ውሎዋ እዛው ነው። ልጅ መውለድ ስላልቻለች አጎቴ ልጅ ፈልጎ ከሌላ የወለዳቸውን ስድስት ልጆች በጥንቆላ አስገድላለች። የሠይጣን ቁራጭ የሆነች ጋኔን የሰፈረባት ሴት ነበረች። እኔን በጣም ትበድለኝ እና ታስርበኝ ነበር። ንብረቴን እንዲወርስ ሆን ብሎ ነው ያመጣው የሚል ቁጭት ስላለባት እኔንም ማጥፋት ትፈልጋለች። ታዲያ እዛው አጎቴ ቤት ሠራተኛ የነበረች ደሜ የምትባል መልካም ሴት ነበረች። ለእኔ መቼም ምንጊዜም የማልረሳት ባለ ውለታዬ ነበረች፡ የአጎቴ ሚስት ከቤት አስወጥታ በር ስትዘጋብኝ ይኽቺ ደሜ የምትባለው ሠራተኛ የሚበላ ነገር ደብቃ በአጥር በኩል ቀስ ብላ ታቀብለኛለች። ሊዮን የሚባለው ግዙፍ የአጎቴ የጀርመን ውሻ በጣም ስለሚወደኝ ከኔ ጋር ውጪ ተኝቶ ሲጠብቀኝ ያድራል። 
.
ጋዜጠኛ፡- ለምን ይኽን በደልህን ለአጎትህ አትናገርም ነበር? 
.
ሙሉቀን፡- እሱ የት ተገኝቶ? የት ውሎ የት እንደሚያድር አላውቅም። የሥራ ጠባዩ ስለሆነ ብዙ ጊዜ እቤት አይመጣም ድንገት ከመጣም እኔ በግል እንዳላነጋግረው አጋጣሚውን ሁሉ ትደፍንብኛለች። እኔ ሕፃን ነኝ፤ በደል በጣም ሲበዛብኝ ራሴን ማጥፋት ወሰንኩ። ሶስት ጊዜ ራሴን ልሰቅል ከዛፍ ላይ ወጥቼ ሰው ደርሶ አድኖኛል። በልጅነቴ የደረሰብኝ በደል በተለይ የጎሹ አባት የሚባሉ አዛውንት ብዙ ጊዜ ተከታትለለው ከሞት አትርፈውኛል። ኑሮ በጣም መሮኝ ነበር፤ በዚህ ላይ ቤተሰቦቼ ይናፍቁኛል። ለሁሉም ነገር መፍትሔ ስላጣሁለት ነበር ራሴን ማጥፋት የመረጥኩት። 
.
ጋዜጠኛ፡- ይኼ በጣም የሚያሳዝን ታሪክ ነው። ለመሆኑ ከዛ ሁሉ ስቃይ እንዴት ተገላግለህ እኛ የምናውቀውን ሙሉቀንን ለመሆን በቃህ? 
.
ሙሉቀን፡- አሁንም አትቸኩልብኛ! ልነግርህ እኮ ነው። 
.
ጋዜጠኛ፡- መጨረሻው ናፈቀኝ። ይቅርታ! 
.
ሙሉቀን፡- አንድ ቀን የሠፈራችን ሕፃናት ጳውሎስ የሚባል ትምህርት ቤት ኃይለስላሴ ገንዘብ ይሰጣሉ እያሉ ሲያወሩ ሰምቼ እኔም ከጃንሆይ ገንዘብ ልቀበል ወደዚያው ስሮጥ ሄድኩና ከሌሎቹ ጋር ተቀላቅዬ ተሰለፍኩ። ለነገሩ ሁሉም አንዴ ብቻ ተቀብሎ ይሄዳል እኔ ግን ሕጉን ስለማላውቅ ከተቀበልኩ በኋላ ብሩን ኪሴ ከትቼ እንደገና ከኋላ ሄጄ እሰለፍ እና እቀበላለሁ። የጃን ሆይ አጃቢዎች እና ፖሊሶች ሊያስጥሉኝና ሊከለክሉኝ ሲሞክሩ ጃንሆይ ተውት ይላሉ። በመጀመሪያ ቀን ብዙ ብር ወደ ሰላሳ ብር የሚሆን ተቀብዬ ገባሁ። በጣም ደስ አለኝ። የበለጠ ገንዘብ ለማግኘት ሎተሪ ሁሉ እገዛ ነበር። (የአንድ መልአክ ስም ጠቅሶ)የሌባ ሽርክ ነው ሲባል እሰማ ስለነበር (የሚጠቅሰው መልአክ ስም) እየሄድኩ ሎተሪ እንዲደርሰኝ እፀልያለሁ፣ እሳላለሁ። የምፀልየው ደግሞ በአባቴ ስም ነው፤ ግን አንድ ጊዜም ደርሶኝ አያውቅም። እኔም (የሚጠቅሰው መላክ ስም) ተሳድቤ፣ (የሚጠቅሰው መላክ ስም)) ተሳድቤ እግዚአብሔር የለም እያልኩ እሄዳለሁ። 
.
ጋዜጠኛ፡- ይኽን በምታደርግበት ጊዜ የስንት ዓመት ልጅ ትሆናለህ? 
.
ሙሉቀን፡- እድሜዬ የዛን ጊዜ ሰባት ወይም ስምንት ቢሆን ነው። 
.
ጋዜጠኛ፡- ታዲያ እኮ ሎቶሪ ቢደርስህም አይሰጡህም ነበር። ሎቶሪ ተጫውቶ ለማሸነፍ የእድሜ ገደብ አለው? 
.
ሙሉቀን፡- እሱን እንኳን አላውቅም እኔ ሎቶሪ ገዝቼ ከደረሰኝ ሃብታም እንደምሆን ነው የማስበው። 
.
ጋዜጠኛ፡- ወደ ሙዚቃ ዓለም የወሰደህ መስመር እንዴት ተከፈተ? 
.
ሙሉቀን፡- ብዙም ሳንቆይ አንድ ቀን ኮልፌ አጠና ተራ የአባት ጡረተኞች እና ወላጅ ያጡ ሕፃናትን የሚቀበሉ አሉ ሲባል ወሬ ሰማሁና ሄድኩ። ነገሩ እውነት ነበር ብዙ ችግር ሳይገጥመኝ ወዲያውኑ ተቀበሉኝ። ትምሕርት ቤቱ አዳሪ ነው። የተደራረበ አልጋ ላይ እንተኛለን። የሚቀርብልን ምግብ የሽሮ ዓይነት ነው። የሽሮ ቀይ ወጥ እና የሽሮ አልጫ፤ ሁሉም ነገር ሽሮ በሽሮ ነው። የግድ ሆነና እዛው ኑሮን ተያያዝኩት፤ ዞሬ መግቢያ አገኘሁ። ከጊዜ በኋላ ታዋቂ የሆኑ አርቲስቶች ሁሉ እዛው ነበሩ። 
.
ጋዜጠኛ፡- እነማን እንደሆኑ ትዝ ይልሃል? 
.
ሙሉቀን፡- እነ ፋንቱ ማንዶዬ፣ ግርማ ወልደሚካኤል፣ ቁምላቸው (በኋላ ትራምፔት ተጫዋች የሆነ) ብቻ የሌሎቹ ሥም ተረስቶኛል እንጂ ሌሎችም ነበሩ። 
.
ጋዜጠኛ፡- የአዳሪ ትምህርት ቤት ሕይወትህ እንዴት አበቃ?
.
ሙሉቀን፡- የዚያን ት/ቤት የበላይ ጠባቂ የነበሩት የከንቲባ ዘውዴ ገብረሕይወት ባለቤት ወ/ሮ ደብረ ወርቅ ይባላሉ። ባለቤታቸው ከንቲባ ዘውዴ ቢትወደድ ተብለው የህግ መወሰኛ ምክር ቤት አባል ነበሩ። በትምህርት ቤቱ ውስጥ የምታወቀው በመዝሙር ችሎታዬ ነው። ት/ት በተለይ ሂሳብ የሚሉት ነገር አይሆንልኝም። ታዲያ አንድ ቀን የት/ቤቱ የበላይ ጠባቂ ወ/ሮ ደብረወርቅ ይመጣሉ ተባለና ተማሪዎች በሙሉ ተሰልፈን መጠበቅ ጀመርን። እኚሁ ሴት እኛ በሰልፍ ላይ እያለን ትምሕርት ቤቱን ጎበኙና ወደ እኛ ሲመጡ ዓይናቸው እኔ ላይ አረፈና አስጠሩኝ። ‹‹ይኼ የማነው ቆንጆ? ምን ሆኖ እዚህ ገባ?›› ብለው ጠየቁ። ‹‹እናት እና አባት የለኝም ብሎ ስለ ነገረን ተቀበልነው›› ብለው ነገሯቸው። በጣም አዘኑልኝ። አንዳንድ ነገር አዘጋጅቼለት እኔ ወስጄ አሳድገዋለሁ አሉ። ‹ለመሆኑ በትምሕርቱ ጎበዝ ነው? ምን ይወዳል?› የሚል ጥያቄ ለት/ቤቱ ዳይሬክተር ሲቀርቡላቸው፣ ዳይሬክተሩም ‹‹እሱ የሚወደው መዝሙር እና ሙዚቃ ብቻ ነው›› አሏቸው። በዚህ ጊዜ ወ/ሮ ደብረወርቅ ‹‹ወደ ውጪ ልኬ እንዲማር አደርጋለሁ›› አሉና የእለቱን ጉብኝታቸውን ጨርሰው ሄዱ። በሳምንቱ ተመልሰው ሲመጡ ለእኔ ሹራብ፣ ሸሚዝ፣ ሱሬ እና ጫማ ይዘውልኝ መጡ። ሙዚቃ የሚወድ ከሆነ ከሌሎች እንደዚህ ያለ ፍላጎት ያላቸው ልጆች እንዲመለመሉ ትዕዛዝ ሰጥተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ከጀርመን አገር የሙዚቃ መሣሪያ መጥቶልኝ አቶ ተፈራ አቡነ ወልድ የሚባል የሙዚቃ መምሕር ተመድቦልን ሙዚቃ መማር ጀመርን። 
.
ጋዜጠኛ፡- ለመሆኑ ከሌሎች አብረውህ ከነበሩ ተማሪዎች ጋር የነበረህ ግንኙነት እንዴት ነበር? 
.
ሙሉቀን፡- ጥሩ አልነበረም። 
.
ጋዜጠኛ፡- ለምን? 
.
ሙሉቀን፡- ይቀኑብኛል። 
.
ጋዜጠኛ፡- በምንድን ነው የሚቀኑብህ? በመልክህ? በዘፈን ችሎታህ? ቅናቱ ከምን የመነጨ ነው? 
.
ሙሉቀን፡- አላናግር አልከኝ እኮ! 
.
ጋዜጠኛ፡- ቃለ መጠይቅ ህግ አለው። እኔ እጠይቃለሁ አንተ ትመልሳለህ። ጥያቄና መልሱ የተያያዘ እንዲሆን ማድረጉ የእኔ ፋንታ ነው። ስለዚህ በመሃል ገብቼ ጥያቄ ሳቀርብ ቅር አይበልህ። 
.
ሙሉቀን፡- ይኼማ ዲክታተርሺፕ ነው፤ እኔ የፈለኩትን መናገር የምችል መሰለኝ። መጀመሪያ አድምጠኝና ወደ ኋላ እየሄድን እናስተካክለዋለን። 
.
ጋዜጠኛ፡- እንደዚያማ አይሆንም፤ ግድ የለህም ቃለ መጠይቁ አይበላሽም። አንተም ማስተላለፍ የምትፈልገው ምንም አይጓደልም። እኔ ስጠይቅ አንተ ከጥያቄው መሠረታዊ ሃሳብ ሳትወጣ መልስ ስጠኝ። 
.
መሉቀን፡- ምን ነበር ጥያቄህ? 
.
ጋዜጠኛ፡- ይቀኑብኝ ነበር ያልከው ቅናቱ ከምን የመነጨ ነበር?
.
ሙሉቀን፡- የሚቀኑብኝ በሁሉ ነገር ነበር፤ በችሎታዬ፣ ወ/ ሮ ደብረ ወርቅ በሚያመጡልኝ ከእነሱ ለየት ያለ ስጦታ፣ በቁመናዬ ጭምር ይቀኑብኝ ነበር። 
.
ጋዜጠኛ፡- ይኼ በቅናት የተጀመረ ነገር መጨረሻው ምን ሆነ?
.
ሙሉቀን፡- በመጨረሻ እነዚህ ልጆች በእኔ ላይ አድመው ልብሴን መስረቅ፣ መደብደብ ጀመሩ፤ እኔም በጣም ተበሳጨሁ። ንብረቴን ሲሰርቁ እጅ ከፍንጅ ስይዛቸው እነሱ ትላልቅ እና ጉልበተኛ ስለሆኑ ይደበድቡኛል። በመጨረሻ እኔም አፀፋውን መመለስ ፈለኩና የእነሱን ልብስ መውሰድ ጀመርኩ። “ሌባ ነው፤ ንብረታችንን ሰረቀብን” ብለው ለዳይሬክተሩ ከሰሱኝ። እኔም ትክክለኛውን ነገር ለመናገር ብሞክርም የእነሱ ድምፅ ብዙ ስለሆነ የሚያምነኝ አጣሁና ከትምሕርት ቤቱ ተባረርኩ። 
.
ጋዜጠኛ፡- ወ/ሮ ደብረ ወርቅ ሰምተው ከመባረር ሊያድኑህ አልቻሉም? 
.
ሙሉቀን፡- በኋላ ሰምተው ይሆናል። እኔ ግን ርቄ ስለሄድኩ የተፈጠረውን ነገር አላውቅም። 
.
ጋዜጠኛ፡- ይህ በሚሆንበት ወቅት እድሜህ ስንት ይሆናል? ከዚያስ ምን ሆነ?… ወደ ሙዚቃው ዓለም ወደ ወሰደህ ጎዳና ይዘከን እንደምትሄድ እገምታለሁ። 
.
ሙሉቀን፡- አዎ ትክክል ነህ እና ከዚህ በኋላ የምነግርህ ወደ ሙዚቃ ዓለም ከሄድኩበት እና በሩን ከከፈተልኝ የመጀመሪያው ገጽ ነው፡፡ ከትምህርት ቤቱ እንደወጣሁ አንድ ዘመድ ገዳም ሠፈር እንዳለኝ በወሬ ሰምቼ ነበርና ወደዚያው ሄድኩ፡፡ በዛው ሰሞን አንድ ቀን አቡነ ጴጥሮስ ኃውልት አካባቢ አትክልት ተራ ተብሎ በሚጠራው ሠፈር ሻይ ቤት ገብቼ ስጠጣ አንድ ከእኔ በጣም የሚበልጥ ልጅ አርሞኒካ ይጫወታል፡፡ በጣም ጥሩ ችሎታ አለው፡፡ ጠጋ አልኩና "እኔ በድምጼ መዝፈን እችላለሁ እና አንተ ለምን በአርሞኒካ እያጀብከኝ አብረን አንጫወትም" አልኩት፡፡ በዚህ ተስማማንና እኔ ስዘፍን እሱ በአርሞኒካ ሲያጅበኝ ሻይ ሊጠጣ የመጣው ሰው ሁሉ ማጨብጨብና ማድነቅ ጀመረ፡፡ የሻይ ቤቱም ባለቤት ገበያ ሲበዛ በጣም ደስ አለውና እዛው እንድንጫወትለት ለመነን፡፡ እኛም የምንበላው ፓስቴ እና ጮርናቄ እንደልብ ይሰጠናል እና ሻይ ያለገደብ እንጠጣለን፡፡ በጣም ተደሰትን፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- ገንዘብ አይሰጣችሁም? 
.
ሙሉቀን፡- አይመስለኝም ትዝ አይለኝም እና ፓስቴና ሻይ ግን እንደልብ ነበር፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- ከዚህ ልጅ ጋር አብራችሁ ቀጠላችሁ ወይስ ይሔ ሁኔታ ሌላ በር ከፈተልህ? 
.
ሙሉቀን፡- እንግዲህ ልጅነት ላይ ስለነበርኩ ዋናው የእኔ ትግል የቀን ምግቤን መሸፈን ስለነበር በሱ በኩል ተሳክቶልኛል፡፡ በዛው ዓመት ጥምቀት በዓል ላይ ከዚሁ ልጅ ጋር በየታቦቱ እየዞርን እንጫወት ጀመር፡፡ ሰው ሁሉ በእጅጉ ተደነቀ፡፡ "ይህ ልጅ ወደፊት ጥላሁንን የሚበልጥ ነው" ተባለ፡፡ ተመልካቹ በሙሉ ገንዘብ ይሰበስብና ይሰጠናል በቃ ምን ልበልህ ተደሰትን፡፡ አንድ ቀን ጨዋታችንን ጨርሰን ሌላ አንድ አብሮን የዋለ ጓደኛዬን ልንሸንኝ በደጃች ውቤ ሠፈር በኩል ስንሄድ የማየው መብራት ሁሉ ገነት የገባሁ መሰለኝ፡፡ ምሽት ስለነበር ሁሉም ቡና ቤቶች የተለያየ ቀለም ያላቸው መብራት አብርዋል፡፡ እኔ ደግሞ እንደዚህ ዓይነት ነገር በሕይወቴ አይቼ አላውቅም፡፡ በቃ የገነት በር መሰለኝ፡፡ ለካ ገሃነም እሳት ነበር፡፡ እነዚህን ቡና ቤቶች አንድ ሱቅ ተጠግተን ስናይ ታኮ ጫማ ያደረጉ ሴቶች ወዲያ ወዲህ ይላሉ፡፡ ትዕይንቱ ሁሉ አስደሰተኝ፡፡ ቀስ ብለን ባለሱቁን፡- “ይኼ ምንድን ነው?” ብለን ጠየቅነው፡፡ “ይኽማ ፓትሪስ ሉሙምባ የሚባለው የታወቀ ናይት ክለብ ነው” አለን፡፡ የሚዘፍኑትስ ሙዚቀኖች እነማን ናቸው? አልነው፡፡ “ፈጣን ባንድ ይባላሉ” አለን፡፡ እዚህ የሙዚቃ ባንድ ውስጥ እነ አያሌው መስፍን እና ሌሎች የታወቁ ዘፋኞች አሉበት፡፡ አያሌው መስፍን ዘፈን ይችላል፤ በቴሌቭዥን አይቼዋለሁ፡፡ ጓደኛዬ ቀበል አደረገና “እሱ ዘፈን በጣም ይችላል& አይቀጥሩትም?” የሚል ጥያቄ አቀረበ፡፡ “ባለቤቷ ወ/ሮ አሰገደች አላምረው ይባላሉ፡፡ በጣም ደግ ሴት ናቸው፡፡” አለን፡፡ እባክህ ወረቀት እንዳለህ ስጠኝና ደብዳቤ ልፃፍላቸው አልኩና በሰጠኝ ወረቀት ላይ “አሳዳጊ ወላጅ እና መኖሪያ የሌለኝ የደሃ ልጅ ነኝ መዝፈን ግን በደንብ እችላለሁ፤ እባክዎ ይቅጠሩኝ፡፡” ብዬ ፃፍኩና ለእሳቸው እንዲያደርስልኝ ለዘበኛው ብሰጠው ሰድቦ አባረረኝ እኔም ማልቀስ ጀመርኩ እና እሱም በዱላ ከአከባቢው ሊያርቀኝ ሲል መጯጯሁን የሰሙት ወ/ሮ አሰገደች አላምረው ድንገት ሁኔታውን ተመልክተው ምን ሆኖ ነው የሚያለቅሰው ብለው ወደ እኔ ሲጠጉ የሆነውን ነገር ነገርኳቸው፡፡ የዚህ ጊዜ ሁኔታዬን አይተው “ይሄማ ኤልቪስን አይደል እንዴ የሚመስለው?” አሉና በኃዘኔታ አባበሉኝ፡፡ እኔም እባክዎ ጥሩ ድምፅ አለኝ ይቅጠሩኝ አልኳቸው፡፡ ዘመድ የለህም ብለው ሲጠይቁኝ ሲሉኝ ከጎጃም አምጥተው ሜዳ ላይ ጣሉኝ ማንንም አላውቅም አልኩ፡፡ ከልባቸው አዘኑልኝና ስዩም የሚባለውን የኦርኬስትራውን ኃላፊ አስጠርተው እንዲፈትነኝ ነገሩት፡፡ እሱም የድምጽ ችሎታዬን ተመልክቶ በጣም በመደነቁ በኦርኬስትራው ታጅቤ እንድጫወት አደረገ፡፡ “ምግብማ ሞልቷል” የሚለውን የጥላሁንን ዘፈን ከእነ አክሽኑ በደንብ ሰለምችል እና ዘፈኑን ስጨርስ ቤቱ በሙሉ ጭብጨባ በጭብጨባ ሆነ፡፡ የኦርኬስትራው ሙዚቀኞችም በጣም ከመደሰታቸው የተነሳ አለባበሴን አይተው ወዲያው ገንዘብ አዋጡልኝ፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- ምን ነበር በወቅቱ የለበስከው? 
.
ሙሉቀን፡- አንድ ቤዥ ቀለም ቁምጣ ሱሪ ነበረችኝ በሷ ላይ ስቀደድ ቀይ ስለጥፍባት እና እንደገና ስትቦጨቅ አረንጓዴ ስጥፍባት ማንነቷን ቀይራ ቀለሟም አያስታውቅም፡፡ ጫማ የለኝም ባዶ እግሬን ነኝ፡፡ ባለቤቷ ባዩት እና በሰሙት ነገር ተደንቀው አምጡት አሉና ራት እንድበላ ከሁሉም ዓይነት ቀረበልኝ፡ ልዩ ክፍል ተዘጋጀልኝና የግል ባኞ ቤት ተሰጠኝ፡፡ በዛው ምሽት እዛ ክለብ ውስት ከሚሰሩት ሴቶች 260 ብር ተዋጣና ልብስ ይገዛለት ተባለ፡፡ እኔ ይኼን የገንዘብ ልክ በቁጥር እንጂ በዓይኔ አይቼ አላውቅም፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- ያቺ ምሽት ናት ማለት ነው ህይወትህን የቀየረችው?
.
ሙሉቀን፡- ቆይ እንጂ ታሪኩ ብዙ ነው አታጣድፈኝ፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- ሌላውን ቀስ እያልን እደርስበታለን፡፡ የሕይወትህ መቀየር የታየበት ቀን ማለቴ ነው? 
.
ሙሉቀን፡- ሕይወቴን የቀየረውማ ጌታ እየሱስ ነው፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- አሁን ወደ መንፈሳዊ ሕይወትህ ስላልገባን እሱ ይቆየንና ወደ ሙዚቃ ዓለም ለመግባት በር ከፋች የሆነውን ነው የጠየኩህ? 
.
ሙሉቀን፡- ዋናው ነገር ወ/ሮ አሰገደች አላምረው ለእኔ አዝነው አስጠግተውና መኖሪያ ሰጥተው የመጀመሪያ ሕይወቴ እንዲቀይር የደረጉት እሳቸው ናቸው፡፡ ውለታቸውን ሳልመልስ መሞታቸው ይቆጨኛል፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- አርሞኒካ አብሮህ ይጫወት የነበረውስ ልጅ የት ደረሰ?
.
ሙሉቀን፡- በቃ ተለያየን እና እሱም እንጀራ ፍለጋ ወደመራው ሄደ እና እኔም በገጠመኝ ነገር ቀጠልኩበት፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- እስኪ ባጭሩ የፓትሪስ ሉሙምባ ናይት ክለብ፤ የፈጣን ኦርኬስትራ እና ያንተ ሕይወት ምን ይመስል እንደነበር አጫውተን? 
.
ሙሉቀን፡- ለጥቂት ቀናት በዱሮ ልብሴ መድረክ ላይ መጫወቴ ትዝ ይለኛል& ከዛ በኋላ ግን ሌላ ክለብ የሚሄዱ ሰዎች ሁሉ እኔ ወዳለሁበት መጉረፍ ጀመሩ፡፡ ዝናዬ ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ ተሰማ፡፡ ተወዳጅነቴ በአጭር ጊዜ ታወቀ፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- ወ/ሮ አሰገደች እንደልጅ ይመክሩህ ነበር? 
.
ሙሉቀን፡- በጣም እንጂ ለምሳሌ ሰዎች መጠጥ ሰጋብዙኝ ገንዘብ ይሁንልኝ ለስላሳ መጠጥ አልፈልግም በል ይሉኛል፡፡ እኔም እንደዛ እያልኩ ገንዘብ በገንዘብ ሆንኩ፡፡ ኑሮዬ በአፋጣኝ ተለወጠ፡፡ ሰው ሁሉ ወደደኝ፡፡ የሌላው ክለብ እየቀዘቀዘ የእኛ ክለብ እየሞቀ መጣ፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡-ገንዘብ ስታገኝ አገር ቤት ያሉ እህቶችህን መርዳት ጀመርክ ወይስ እድሉን አላገኘህም? 
.
ሙሉቀን፡- ብር አጠራቅሜ ልኬ ከጎጃም እህቶቼ መጥተው ነበር፤ ስዘፍን አይተውኛል፡፡ ሴትዮዋም አህቶቼን ጠርተው “ይሄ ልጅ ከዚህ በኋላ እኔ ጋ ይኖራል በወር ዘጠና ብር እሰጠዋለሁ” አሏቸው፡፡ ዘጠና ብር በዚያን ጊዜ በጣም ብዙ ገንዘብ ነበር፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- የዛን ጊዜ እድሜህ ስንት ይሆናል? 
.
ሙሉቀን፡- 11 ወይም 12 ቢሆነኝ ነው፡፡ 
.
ጋዜጠኛ:- ከወ/ሮ አሰገደች አላምረው እና ከፈጣን ባንድ ጋር እንዴት ተለያያችሁ? 
.
ሙሉቀን፡- የተለያዩ ኦርኬስትራዎች እኔን ለመውሰድ ጨረታ ገቡ፤ ሁሉም ያባብሉኝ ጀመር፡፡ የዛን ጊዜ በከተማው ታዋቂ ከሆኑት ባንዶች አንዱ የዙላ ባንድ ነበር፡፡ እነተሾመ ምትኩ የሚጫወቱት እዛ ነው፡፡ በፊት ተሾመ ሲጫወት በቴሌቭዥን አይቼዋለሁ፡፡ ጎበዝ ዘፋኝ ነው፡፡ የዙላ ክለብ ሲያግባባኝ “ይህቺ ... በ90 ብር ባሪያዋ አደረገችህ አይደል እኛ 300 ብር እንከፍልሃለን ጥለሃት ወደ እኛ ና” ብለው አግባቡኝ፡፡ከዛምጠፍቼ ወደ ዙላ ባንድ ሄድኩ፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- ወ/ሮ አሰገደች ሲሰሙ ምን ተሰማቸው? 
.
ሙሉቀን፡- እንደሰሙ እብድ ሆኑ እና ኮንትራትና ውሉን አፍርሷል ብለው ፍርድ ቤት ከሰሱኝ፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- ተመለስክ ወይስ በዛው ቀረህ? 
.
ሙሉቀን፡- አልተመለስኩም ከዙላ ጋር መስራት ጀመርኩ፡፡ ዙላ ክለብ ምግብና መኖሪያ ይሰጥሃል እና ገንዘብ ግን አይሰጥህም፡፡ የገቡትን ቃል ሁሉ አላከበሩም፡፡ ውሸታቸውን ነው፡፡ ባለቤቱ በጣም መጥፎ ሰው ነው፡፡ እዛ የተጫወቱት ሙዚቀኞች ደግሞ ሥራቸውን መጠጣት እና መስከር ብቻ ነው፣ ሥነ ሥርዓት የሚባል ነገር የለም፣ ኑሮው ሁሉ የዱርዬ ዓይነት ሆነብኝ፣ እኔም ደስተኛ አልነበርኩም፡፡ በዚህ መሐል ከፖሊስ ኦርኬስትራ አለማየሁ እሸቴ በሆነ ምክንያት ጥሎ ይወጣል፡፡ ኮሎኔል ታዬ ባለኬር እና ሻለቃ ወርቅነህ ዘለቀ ወደ እኔ መጥተው እኛ በወር 300 ብር እንከፍልሃለን ብለው ወሰዱኝና በሲቪል ደንብ ተቀጥሬ ፖሊስ ኦርኬስትራ ገባሁ፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- ለመሆኑ በገባህበት የሙዚቃ ባንድ ሁሉ የምትጫወተው ዘፈን የሌላ ሰው ነው ወይስ የራስህን መጫወት ጀመርክ? 
.
ሙሉቀን፡- ከፖሊስ ሠራዊት ኦርኬስትራ በፊት ጋዜጠኛው ሰለሞን ተሰማ ለእኔና ለተሾመ ምትኩ የሰጠንን “የዘላለም እንቅልፍ እስከሚወስደኝ ፍቅሬ የእኔ እጮኛ መቼም ያንቺው ነኝ” የሚለውን ተጫውቻለሁ፡፡ ፖሊስ ሠራዊት ደግሞ “እምቧይ ሎሚ መስሎ” የሚለውን ተስፋዬ አበበ የሰጠኝ ዘፈኖች ለዝናዬ በር ከፋቾች ናቸው፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- መቼም ጊዜው ረዥም በመሆኑ ሁሉንም ማስታወስ ሊከብድ ይችል፡፡ ግን ከሌሎች ግጥምና ዜማ ፈጣሪዎች የተሰጡህ ትዝ ይሉሃል? 
.
ሙሉቀን፡- አዎ! “ያላየነው የለም ሁሉንም አይተናል” የሚለውን ዘፈን ግጥሙን ሠይፉ ኃ/ማርያም ዜማውን ደግሞ አቡበከር እሸቴ ሰጥተውኝ በደንብ አድርጌ ተጫውቼዋለሁ፡፡ በወቅቱ በነበረው የዘፈን ምርጫ ፕርግራምም ከፍተኛ ተመራጭነት የያዙ ነበሩ፡፡ “እናቴ ስትወልደኝ መች አማከረችኝ እና የፊት ጉዴን ትታ እደግ ማሞ አለችኝ” እና “ያ ልጅነት በጊዜያቱ ደስ ማለቱ” የሚለውም የተስፋዬ አበበ ድርሰት ነው፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- ለመሆኑ ከፖሊስ ሠራዊት ኦርኬስትራ ጋር እንዴት ከረማችሁ? 
.
ሙሉቀን፡- ቆይ ልንገርህ የእነሱንማ ጉድ፤ ፖሊሶች በጣም ዋሽተውኛል፡፡ የገንዘቡን መጠን ከፍ አድርገው ሦስት መቶ ብር በወር ያሉኝ እኔን በእጃቸው ለማስገባት እንጂ ጭራሽ ውሸታቸውን ነበር፡፡ የክህደታቸው ክህደት ሁለት መቶውን ብር ቆርጠው አንድ መቶ ብር በወር ይከፍሉኝ ጀመር፡፡ ምነው እንዲህ ታደርጋላችሁ ነውር አይደል ወይ ብዬ ብጠይቅ የሁሉም ደመወዝ ከዚህ ያነሰ ነው እና ለአንተ ነው ከፍተኛውን ደመወዝ የምንከፍለው ለወደፊቱ ደግሞ ይጨመርልሃል ብለው አግባቡኝ፡፡ እኔ ግን ከፍተኛ ቅሬታ ተሰማኝ፡፡ የፖሊስ ኦርኬስትራንም በጣም ጠላሁት፡፡ ሌላው የኦርኬስትራው ችግር ደግሞ ሠርግም ይሁን ሌላ ትልቅ ዝግጅት ከኛ ጋር ሲሰሩ የነበሩትን የኦርኬስትራው አባላት ቀን ሙሉ ሲሰሩ ውለው ማታ ዘብ ያቆሟቸዋል፡፡ ይኼ ሁሉ ተጨምሮ ነው የበለጠ እንድጠላቸው ያደረገኝ፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- በውስጥህ ሙዚቃ ብቻ ሳይሆን ሰብዓዊነትና ለሌላው ተቆርቋሪነት አለብህ ማለት ነው?
.
ሙሉቀን፡- አንተ ታሾፋለህ መሰለኝ? 
.
ጋዜጠኛ፡- ይኼ ማሾፍ ሳይሆን አንተነትህን መግለጽ መሰለኝ፡፡ 
.
ሙሉቀን፡- እውነትን ለመናገር እኔ ከልጅነቴ ጀምሮ ለሌላው መቆርቆርና ሰብዓዊነት በውስጤ ምንጊዜም አለ፡፡ እኔ ላይ ካልደረሰ ብዩ ሌላው ሲጠቃ ዝም ብዬ ማየት እልችልም፡፡ ይኼ ተፈጥዬ ነው፤ እስካሁንም አብሮኝ ይኖራል፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- ይኼን እናሳጥረው እና ወደ ሌላው ብንሸጋገር ምን ይመስልሃል? 
.
ሙሉቀን፡- ለምንድነው ወደሌላ የምንሸጋገረው? ይኼን እንጨርስ እንጂ፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- ሙሉቀን! ባንተ ህይወት ውስጥ ያለፍክበትን እያንዳንዱ ነገር የምንነጋገርበት ከሆነ እንኳን መፅሄት አንድ መፅሐፍም ላይበቃ ነው፡፡ ስለዚህ ሁሉንም ነገር አጠር አድርገን መነጋገር ሊኖርብን ግድ ይላል፡፡ ግድ የለህም በእኔ ይሁንብህ ታሪኩ አይበላሽም ቁም ነገሩንም አልስተውም፡፡ 
.
ሙሉቀን፡- እስቲ እናያለን ቀጥል ጥያቄህን? 
.
ጋዜጠኛ፡- ከፖሊስ ሠራዊት አርኬስትራ ጋር እንዴት ተፋታችሁ? ምን ያህል ጊዜስ አብረህ ሰራህ? 
.
ሙሉቀን፡- ሁለት ዓመት ተኩል አካባቢ እንደሰራሁ አንድ ቀን የፖሊስ ዩኒፎርም እንደለበስኩ ወጥቼ በዛው ቀረሁ፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- ለመሆኑ መለዮ ለባሽፖሊስ ሆነህ ነበር እንዴ እኔ እኮ የመሰለኝ በሲቪል ደረጃ የሚያሰሩህ መስሎኝ? 
.
ሙሉቀን፡- የፖሊሶች ትልቁ ችግራቸው መዋሸት ነው፡፡ ውሸታቸው ከዛ ይጀምራል፡፡ ተቀጥሬ ትንሽ እንደቆየሁ ዩኒፎረም መልበስ አለብህ ተባልኩ፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- ማዕረግህ የሚወሰነው በምን ነበር በደመወዝ ወይስ በምትሰራው ሥራ? 
.
ሙሉቀን፡- እነሱ እባክህ እደፈለጋቸው ነው፡፡ ይህንን እንተወው፤ የያኔዎቹ አሁን ስለሌሉ ወቀሳው ምንም ነገር አያሻሽልም እንተወው፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- እሺ እውነትህን ነው እዚህ ላይ ይኸን እናቁምና ወደሌላው እንለፍ፡፡ ከዚያ በኋላ ያለውን በሙዚቃ የነበረህን ቆይታ ባጭሩ አጫውተን? 
.
ሙሉቀን፡- ይኽ እኮ ባጭሩ የምትለው ነገር ነው እኔ የማልስማማበት፤ የእኔ ሕይወት እና በሙዚቃ ዓለም የሰራሁት ታሪክ በአጭሩ የሚገለጽ አይደለም፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- እሺ በአጭሩ ሳይሆን በረዥሙ አጫውተን? 
.
ሙሉቀን፡- እንደዚያ እየተስማማን ብንነጋገር ይሻላል፡፡ ከዚያ በኋላ ፒያሳ ገብረተንሳይ ኬክ ፊት ለፊት ያለው “ቬኑስ ክለብ’’ ገባሁ፡፡ በወቅቱ በጣም ታዋቂና ተወዳጅ ክለብ ነበር፡፡ ከቬኑስ ጋር ለጥቂት ጊዜ ሰርቼ ወደ ዋቢሸበሌ ገበሁ፡፡ ከዚያ በኋላ ጥቂቶች ተሰባስብንና “ኢክዌተርስ” በሚል ባንድ ጊዮን ሆቴል እንሰራ ጀመር፡፡ እንግዲህ የእኔ ሕይወት ሙሉ በሙሉ የተለወጠው የዛን ጊዜ ነው፡፡ እነ “ሠውነቷ፣ ናኑ ናኑ ናዬ፣ አገሯዋሳ መገና” ሁሉ የወጡት የዛን ጊዜ ነው፡፡የሠይጣን ዘመን ነበር ጊዜው፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- እዚህ ላይ አንዴ ላቋርጥህና ለምን እንዲህ ልትል ቻልክ? 
.
ሙሉቀን፡- እንደዚህ ምን? 
.
ጋዜጠኛ፡- ዘመኑ የሠይጣን ነበር ማለትህ ነዋ፡፡ እንደኔ ከሆነ ወርቃማ ዘመንና ዘመናዊ ሙዚቃ በሃገራችን ያበበበት እና እንደ አንተ ዓይነቱ ድምፃዊ የፈራበት ወቅት ነበር፡፡ 
.
ሙሉቀን፡- እሱ ላንተና ለመሰሎችህ ነው፡፡ ለእኔ ሠይጣን ለጉሞኝ እንደፈለገው ሲጋልበኝ የነበረበት ወቅት ነበር፡፡ አንተ የፈለከውን በል እኔ ‹‹የሠይጣን ዘመን›› እለዋለሁ፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- አንተ ዘፋኝ በመሆንህ ነው የሠይጣን ዘመን ያልከው? 
.
ሙሉቀን፡- አዎ! ዘፈን የሠይጣን ነው፡፡ ዘፋኝ ገነት አይገባም ይላል መፅኃፉ፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- እሱን ወደ ኋላ እንመጣበታለን፡፡ እስቲ በዚያን ወቅት ታዋቂ ስለነበሩት አርቲስቶች ትንሽ አጫውተን? 
.
ሙሉቀን፡- በወቅቱ ታዋቂ የነበርነው እኔ ምኒሊክ ወስናቸው እና ጥላሁን ገሠሠ ነበርን፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- ለመሆኑ የምታደንቀው እና ለአንተ ጥሩ ምሳሌ የሆነህ ድምፃዊ ማነው?
.
ሙሉቀን፡- እኔ በሀገራችን ከተፈጠሩ ድምፃውያን ውስጥ በጣም የማደንቀው በአንደኛ ደረጃ ምኒሊክ ወስናቸውን ሲሆን ከዚያ ቀጥሎ ተሾመ ምትኩን እና ማህሙድን ነው፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- ጥላሁንን የረሳኸው መሰለኝ፡፡ 
.
ሙሉቀን፡- አልረሳሁትም፡፡ ጥላሁን ለእኔ ዘፋኝ አይደለም፡፡ ድምፅ እንጂ ታለንት የለውም፡፡ የመድረክ ብቃትም የሌለው ሰው ነው፡፡ እኔ ጥላሁን ገሠሠን እንደ ታላቅ አርቲስት ቆጥሬውም አላውቅም፤ አይደለም፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- ሙሉቀን ምን ማለትህ ነው? ጥላሁን በሠላም ጊዜ ሕይወትን፣ ፍቅርን፣ ደስታና ኃዘንን በዜማው እና በዘፈኑ የገለፀ ድምፁ በሁሉም ዘንድ የተወደደ ዝነኛ እና ብቸኛ አርቲስት ነው ፡፡ ለዚህም የረጅም ጊዜ መልካም አገልግሎቱ ከተለያዩ ሽልማቶች አንስቶ የክብር ዶክትሬት እእስከማግኘት በቅቷል፡፡ ታዲያ አንተ አርቲስት አይደለም ብለህ ስትል ይኽን ታላቅ ሰው ማቃለል አይሆንም? 
.
ሙሉቀን፡- አየህ ስህተቱ የሚጀምረው እዚህ ጋ ነው፡፡ ሙዚቃ መስማት እና ማወቅ በጣም የተለያዩ ነገሮች ናችው፡፡ እናንተ ሙዚቃ በጆሯችሁ መስማት ነው የምታውቁት እኔ ደግሞ ሙዚቃን በደንብ መለየት እችላለሁ፡፡ ከዚህ ጋር አብሮ መታየት ያለበት ደግሞ የመድረክ አጠቃቀም እና ብቃት ነው።
.
ጋዜጠኛ፡- ምን ማለት ነው እስቲ ግልፅ አድርግልን? 
.
ሙሉቀን፡- አታቻኩለኛ!... ልነግርህ እኮ ነው! የመድረክ ብቃት ማለት አንድ አርቲስት በመድረክ ሲጫወት ከሚያጅቡት ሙዚቀኞች ጋር መናበብና መደማመጥ ከእነሱም ጋር ድምፁን አስማምቶ መጫወት ማለት ነው፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- ታዲያ ጥላሁን በዚህ በኩል ችሎታ የለውም ነው የምትለኝ? ቅሬታስ ያሰማ የሙዚቃ አጃቢስ አለ? 
.
ሙሉቀን፡- አሁንም አላስጨረስከኝም! ጥላሁን የጉልበት ዘፋኝ ነው፡፡ ያቺ በተፈጥሮ የተሰጠችውን ድምፅ በጣም ስለሚኩራራባት አጃቢዎቹን በጣም ይንቃል:: በአብዛኛው ከሙዚቃ ውጭ ወደፊት ወይም ወደኋላ በመሄድ አጃቢዎቹን በጣም ያስጨንቃል ግራ ያጋባል፡፡ እሱ የሚያየው አፉን መክፈቱን ነው እንጂ የአጃቢ ሙዚቀኞቹን ምቾት አይጠብቅላቸውም፡፡ ይኼ ደግሞ ብዙ ጊዜ ስሞታ አስከትሎበታል፤ ግን የሚያዳምጥ የለም፡፡ ጥላሁን.. ጥላሁን ስለተባለ ብቻ ሁሉም ለእሱ ያደላል የአጃቢ ሙዚቀኞቹን ስሞታ የሚሰማ የለም፡፡ እነሱም ሥራችንን በዚህ ምክንያት እናጣለን በማለት እንደምንም እሱን ለመከተል ይገደዳሉ፡፡
.
ጋዜጠኛ፡- ለመሆኑ ከጥላሁን ጋር በሙያችሁ የነበራችሁ ግንኙነት እንዴት ነበር? 
.
ሙሉቀን፡- እንደ ማንኛውም ዘፋኝ አብሬው ሰርቻለሁ፡፡ ግን የመድረክ ብቃቱን አልወድለትም ነበር፡፡ መቼም ይኽንን በምልበት ጊዜ ብዙዎች ቅር እንደሚሰኙ ይገባኛል፡፡ ሁሉም እሱ ላይ የአምልኮ ወይም ካለሱ በስተቀር ግሩም ዘፋኝ የለም የሚል እምነት ሊኖራቸው ይችላል፡፡ እኔ ግን በሙያው ውስጥ ስለነበርኩ ያለምንም ይሉኝታ ነው ስለሁሉም የምናገረው፡፡ ስለዚህ አሁንም ደግሜ ጥላሁን ድምፅ እንጂ አርቲስት የሚለውን ሥም የሚያሟላ ታለንት የለውም የምለው፡፡ ደግሞም ትክክል ነኝ፡፡ 
.
ጋዜጠኛ፡- ለመሆኑ ከድምፃዊነት ባሻገር ሌላ ምን ችሎታ አለህ?
.
ሙሉቀን፡- የእኔ ችሎታ ጥቂት አይደለም፡፡ ጥምር የሆነ የብዙ የሙዚቃ አይነቶች ባለቤት እና ችሎታውም ያለኝ ሰው ነኝ፡፡ የእኔን ያህል በሙዚቃው አለም ብዙ እውቀት ያለውም በሃገሪቱ አልተፈጠረም አሁንም የለም ይሄንን በማስረጃ ለማረጋገጥ ሙዚቃ እፅፋለው፣ ግጥም እደርሳለሁ፣ ሙዚቃና ዜማውን ኮምቦዝ አደርጋለሁ፣ ድራም በደንብ እጫወታለሁ በዚህ ላይ ደግሞ ድምፃዊ ነኝ፡፡ እስቲ እነዚህን ሁሉ ችሎታዎች የያዘ አንድ አርቲስት ጥራልኝ? ዛሬ እኮ የጠጅ ቤት አዝማሪ ሁሉ አርቲስት እየተባለ የሚጠራበት ዘመን ላይ ደርሳችኋል፡፡
       ከሸገር ታይምስ ጋር ካደረገው ቃለ ምልልስ።
ሙሉቀን ከረጅም ሕመም በኋላ በ70 አመቱ ሚያዝያ 1-2016ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል።

Friday, April 5, 2024

የእስራኤል ጦር ኃይል ለሁለት ሳምንታት ያህል በጋዛው አል-ሺፋ ሆስፒታል ላይ ወረራ ካካሄደ በኋላ አብዛኛውን የህክምና ተቋሙን ክፍል ለቆ መውጣቱ ተገለጸ።

 የእስራኤል ጦር ኃይል ለሁለት ሳምንታት ያህል በጋዛው አል-ሺፋ ሆስፒታል ላይ ወረራ ካካሄደ በኋላ አብዛኛውን የህክምና ተቋሙን ክፍል ለቆ መውጣቱ ተገለጸ።

በሆስፒታሉ ላይ ከተካሄደው ወረራ እና ጥቃት በኋላ የጋዛው ሆስፒታል ሕንፃ አፅሙ ቀርቶ ታይቷል።
የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት እንደገለጸው ወታደሮቹ በመቶዎች የሚቆጠሩ “ሽብርተኞችን” ገድለዋል እንዲሁም በቁጥጥር ሥር አውለዋል።
ሠራዊቱ “በሆስፒታሉ ዙሪያ” የጦር መሣሪያዎች እና የደኅንነት መረጃዎች ማግኘቱን ገልጧል።
በሐማስ የሚመራው የጋዛ ጤና ሚኒስቴር በርካታ ሬሳዎችን ጥሎ ለመሄድ መገገዱን አሳውቋል። የአካባቢው ሰዎች ደግሞ ሥፍራው መውደሙን ይናገራሉ።
የእስራኤል ጦር፤ በአል-ሺፋ ሆስፒታል ላይ ወረራ እና ጥቃት የፈጸመው ሐማስ መልሶ ስለተደራጀበት መሆኑን ይገልጣል።
በእስራኤል አየር ድብደባው ምክንያት በሆስፒታሉ ዙሪያ ያሉ ሕንፃዎችንም ጭምር ያጠቃ ነበር። የእስራኤል ጦር የሆስፒታሉን የሕክምና ክፍሎች ያወደምኩት ሐማስ እና የፍልስጤም ኢስላሚክ ጂሀድ ስለሚጠቀሙበት ነው የሚል መግለጫ አውጥቷል።

An American woman was killed while on a safari in Zambia after an elephant charged their tour group.

 An American woman was killed while on a safari in Zambia after an elephant charged their tour group.

It was supposed to be the "last big adventure" for 79-year-old Gail Mattson, when the vehicle carrying her and five other guests on a game drive in Zambia was attacked by an "aggressive" bull elephantAn elderly American tourist was killed after an "aggressive" bull elephant attacked a vehicle during a game drive in Zambia, the safari operator said.

The incident took place Saturday morning at Kafue National Park, a Lusaka Police spokesperson confirmed to ABC News. Gail Mattson, 79, was confirmed by the family as the victim.

"An aggressive bull elephant charged the vehicle carrying six guests and a guide who were on a game drive from Lufupa Camp," Wilderness, the company operating the safari, said in a statement to ABC News Wednesday..

የኩላሊት ታማሚ በማስመሰል ጓደኛቸውን መኪና ውስጥ አስተኝተው ገንዘብ ሲሰበስቡ የተገኙ 10 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ።

 የኩላሊት ታማሚ በማስመሰል ጓደኛቸውን መኪና ውስጥ አስተኝተው ገንዘብ ሲሰበስቡ የተገኙ 10 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ።

***
ምንም አይነት የጤና ችግር የሌለበት ጓደኛቸውን ሁለቱም ኩላሊቶቹ ከጥቅም ውጪ የሆኑ በማስመሰል በህክምና ሰበብ ገንዘብ ሲያሰባስቡ የነበሩት 10 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር የዋሉት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ልዩ ቦታው አዲስ ሰፈር እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ነው ።
ግለሰቦቹ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3- B21705 አ.አ የሆነ ሚኒባስ ተሽከርካሪን በመጠቀም ገንዘቡን ሲሰበስቡ የቆዩት የኩላሊት ታማሚ ነው ያሉትን ጓደኛቸውን መኪና ውስጥ በማስተኛት ሲሆን በተያዙበት ወቅት ከአምስት ሺህ ብር በላይ ገንዘብ እጃቸው ላይ ተገኝቷል፡፡
በመዲናችን አዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች ተመሳሳይ የድጋፍ ጥያቄዎች ሲቀርቡ የሚስተዋል መሆኑን የጠቀሰው ፖሊስ፤ ነገር ግን ህብረተሰቡ እንዲህ አይነት የማታለል ተግባር የሚፈፅሙ ሰዎች መኖራቸውን ተገንዝቦ ድጋፍ በሚያደርግበት ወቅት ከህክምናው ጋር የተያያዙ አግባብነት ያላቸውን ሰነዶች በማየትና ትክክለኛነቱን በማረጋገጥ ሊሆን እንደሚገባ አሳስቧል፡፡
ዘገባ፡- ሳጅን ጤናው ፈጠነ
All reactions:
2.2K

ግብፅ የግድቡን ሙሌት ለማስቆም ያላት የመጨረሻ እድል..?

 ግብፅ የግድቡን ሙሌት ለማስቆም ያላት የመጨረሻ እድል..?

▪️ግብፃዊው ምሁር የጠቆሙት ዒላማ
የዓባይ:ልጅ
የአለም አቀፍ ውሃዎች እና የግድብ ኤክስፐርት የሆኑት ግብፃዊ ምሁር ዶ/ር መሀመድ ሃፌዝ፣ በህዳሴ ግድቡ ቀሪ የውሃ ሙሌት እንዳይደረግበት ያደናቅፋል ያሉትንና ለግብፅ የመጨረሻው እድል ነው ሲሉ የሰጡትን ሐሳብ እንደ "አረብ-21 ቴሌቪዥን ያሉ ሚዲያዎች እያሰራጩት ይገኛል።
በኳላላንፑር ዩኒቨርሲቲ እየሰሩ የመገኙት ግብፃዊ ፕሮፌሰር ሙሀመድ ሐፌዝ ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድቡን የውሃ ሙሌት ከዚህ በላይ ከቀጠለችበት ሀገራቸው ግብፅ ለከፍተኛ ችጋር ትዳረጋለች በማለት ጎረቤት ሱዳንም ተመሳሳዩ እንደሚገጥማት ጨምረው ተናግረዋል። የግድቡ የውሃ ክምችት የታቀደለት የ 74 ቢሊዮን BCM መጠን እውን ከሆነ ግብፅ ከሚደርስባት ችግር ውስጥ በተለይም በዬዓመቱ የ 15 ቢሊዮን ለውሃ ነክ ግዢዎች ወጪ ትዳረጋለች የሚለው ይገኝበታል።
ከ “አረብ 21” ጋር በነበራቸው ቆይታ “ግብፅ ከኢትዮጵያ ጋር ችግሩን ለመፍታት ለ12 ዓመታት የተደረጉ ድርድሮችና ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች ያለስኬት መቋጨታቸውን ተከትሎ የትኛውም አማራጮች አልቀዋል" ያሉ ሲሆን ጉዳዩን "በተመድ. የፀጥታው ምክር ቤት፣ በአፍሪካ ህብረት፣ በአረብ ሊግ፣ በአውሮፓ ህብረት፤ እንዲሁም በዩናይትድ ስቴትስ በኩል አዲስ አበባ ላይ ግፊት እንዲያደርጉ የተደረጉ ሙከራዎች ኢትዮጵያን ማሳመን አልቻሉም።"
ሃፌዝ አክለውም “ካይሮ ከአዲስ አበባ ጋር በቅርቡ የተደረገውን ድርድር መቀበሏ ስህተት ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ የግድቡን ቀጣይ ስራ ለማከናወንና እና የግድቡን የውሃ ሙሌት ለማከናወን ምቹ አጋጣሚ ያገኘችበት ነው። በዚህም ውሃውን ከኤሌክትሪክ ማምረት ባለፈ ለሌሎች ልማቶችም ወደ መጠቀም ተሸጋግራለች።"
ከዚህ በተያያዘ የግብፁ የመስኖ ሚኒስትር ሃኒ ስወይለም ባለፈው ሳምንት የህዳሴውን ግድብ በተመለከተ አዲስ ለውጥ አለመኖሩንና ወደ ድርድር እንደማይመለሱም የገለፁበትንና፤ ከዚህ ይልቅ የግብፅ መንግስት ግድቡ ችግር በሚከስትበት ወቅት አስፈላጊውን የሃይል እርምጃ የመውሰድ መብት አለው" ማለታቸውን አስመልክተውም ፕሮፌሰሩ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ይኸውም የግድቡ አካል በሆነ አንድ ክፍል ላይ ወታደራዊ ጥቃት ኢላማውን ጠብቆ ሊካሄድ ይገባዋል የሚል ነው።
"አል-ሙፊድ" ላይ ወታደራዊ ጥቃት የመጨረሻው ዕድል ነው
ሃፌዝ እንዳሉት፣ “አሁን ላይ በህዳሴ ግድቡ ላይም ሆነ በኮርቻ ግድቡ Saddle Dam ላይ ወታደራዊ ድብደባ ለማድረግ የማይቻልበት ደረጃ ላይ ነው የሚገኘው። ግድቡ ከ 41 ቢሊዮን ሜትሪክ ኪዩብ ውሃ የያዘ መሆኑ በግብፅም ሆነ ሱዳን ላይ ከፍተኛ ጥፋትና ውድመት የሚያስከትል ይሆናል።
በሁሉም ሀገራት ላይ ምንም ጉዳት የማያስከትለው የጥቃት ኢላማ ነው በማለት ሲናገሩ ግብፃዊው ፕሮፌሰር በዚህኛው ጥቃት ሶስቱም ሀገራት ኢትዮጵያን ጨምሮ ግብፅ እና ሱዳን ላይ ጉዳት የማያስከትል" በማለትም አስገራም ሀተታ ተጠቅመዋል።
ፕሮፌሰሩ አሁናዊው ኢላማ ነው ያሉት የግድቡ ክፍል የውሃ ማስተንፈሻው Spill Way ሲሆን፤ በአምስተኛው የግድቡ የውሃ ሙሌት ላይ የማከማቻ ሀይቁ ከፍታ ከባህር ጠለል በላይ 640 ሜትር ገደማ ይደርሳል ካሉ በኋላ፤ የግድቡ ማስተንፈሻ Spill Way ላይ ኢላማውን የጠበቀ ጥቃት ማድረስ “ማንም ላይ ጉዳት አያደርስም። ሁሉንም(ሶስቱንም ሀገራት) አሸናፊ ያደርጋል። ይህም ማለት ኢትዮጵያ 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ የማጠራቀም ጉዞዋ ይገታል። የግድቡ ሃይቅ ከፍታም የ 640 ሜትር ኢላማውን እንዳያሳካ ያደርጋል። ይልቁንም ኢትዮጵያ ከዚህ በሚተርፋት ውሃ ኤሌክትሪኳን ብቻ ያለ ችግር እያመነጨት ብቻ የምትጠቀም ትሆናለች" ብለዋል። _____||
▪️እንደሚታወቀው የህዳሴ ግድቡ የውሃ ማስተንፈሻ (Spillway)፤ በተለይም "main controlled spillway" የሚባለው ክፍል በግድቡ የ 624.9 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኝ ሲሆን ግድቡ በ 630 እና 640 ሜትር የውሃ ከፍታው ላይ በሚኖረው የሃይል ማመንጨት ተግባር ውስጥ ግልጋሎት ይሰጣል። የድንገተኛ ማስተንፈሻው emergency spillway በግድቡ 642 ሜትር ላይ ሲገኝ open spillway ደግሞ 640 ላይ ነው የሚገኘው።
▪️ግብፃዊ ልሂቃን ቀደም ባሉት አመታት የጥቃት ኢላማ ይሆን ዘንድ ሲጠቅሱት የነበረው የህዳሴ ግድቡ ከፍል የኮርቻ ግድቡ Saddle Dam እንደነበር አይዘነጋም። ይኸው የኮርቻ ግድብ የህዳሴ ግድቡ ከ 90 ሜትር ወይም (590 amsl) በላይ ከፍታ በመጨመር የግድቡ ከፍታ ወደ 145 ሜትር(645 amsl) ማሳደግ የቻለ ነው። ይህም ከግድቡ የማመንጨት አቅም ውስጥ ከ 1 ሺህ 400 ሜጋዋት በላይ ያለውን ጭማሪ ሁሉ ማምጣት የቻለ፤ እንዲሁም የግድቡን የውሃ ክምችት ከ 11 ቢሊየን ሜትር ኪዩብ በላይ በማድረግ ይሆን ነበር ይላሉ ወደ 74 ቢሊየን ሜትር ኪዩብ ከፍ ማድረግ ያስቻለ ነው - የህዳሴው Saddle Dam የኮርቻ ግድብ ..!

‘‘የክብር ዶክትሬት ሽልማት እንጂ ለመጠሪያነት አይውልም!! ረ/ፕ ወይም ተባባሪ ፕሮፌሰር ነን የሚሉትን ሰዎች ዩንቨርሲቲው “አቶ”ነው የሚላቸው::

 ‘‘የክብር ዶክትሬት ሽልማት እንጂ ለመጠሪያነት አይውልም!! ረ/ፕ ወይም ተባባሪ ፕሮፌሰር ነን የሚሉትን ሰዎች ዩንቨርሲቲው “አቶ”ነው የሚላቸው::

====
(ይትባረክ ዋለልኝ)
የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ‘‘የክብር ዶክትሬት ሽልማት እና የዶክትሬት ትምህርት በኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ በፕሮፌሰር ማስረሻ ፈጠነ አቅራቢነት በፕሮፌሰር ሀብታሙ ወንድሙ አወያይነት መጋቢት 26 ቀን 2016 ዓ.ም በዚሁ ርዕሰ ላይ የገለጻና የውይይት መድረክ አዘጋጅቶ ነበር::
በዚህ የገለፃና የውይይት መድረክ ላይ የክብር ዶክትሬት ሽልማትን በተመለከተ በፕሮፌሰር ማስረሻ ፈጠነ ባቀረቡት ሰፊ የጥናት ፅሑፍ እንደገለፁት የክብር ዶ/ር ሽልማት እንጂ ለመጠሪያነት አይውልም:: እንዲሁም ረዳት/ፕሮፌሰር ወይም ተባባሪ/ፕሮፌሰር የሚለውም ስያሜም በጋዜጠኞች ብቻ የሚሰጥ ቅፅል እንጂ ለመጠሪያነት እይውልም በማለት ተናግረዋል:: በኢትዮጵያ የክብር ሽልማት አሰጣጡ በዩንቨርስቲዎች ላይ ያለውን ችግርም በዝርዝር አንስተው ሊያስተካክሉ የሚገባቸውን ጉዳዮችንም በዝርዝር ገልጸዋል::
በተለይ ፕሮፌሰር ማስረሻ የክብር ዶክትሬትን በተመለከተ በፁሁፋቸው ላይ እንደገለፁት ከሆነ
" በየትኛውም አለም "ክቡር ዶ/ር እገሌ" ተብሎ ሲጠራ አይታወቁም :: የክብር ዶ/ር ይህ በእኛ ሐገር ብቻ በጋዜጠኞችና ከአካዳሚያዊ ክበብ ራቅ ባሉ ሰዎች የሚጠራ ሲሆን ለዚህ ክፍተት ደግሞ የክብር ዶ/ር የሚሸልሙ ዩንቨርሲቲዎቹ የክብር ዶ/ር ለመጠሪያነት እንደማይውል ለተሸላሚዎቹና ለህዝቡ አለመግለፃቸውን እንደችግር አንስተዋል:: አያይዘውም ለነገሩ ረ/ፕ እና ተባባሪ ፕሮፌሰር የሚል መጠሪያ የሚሰማው በእኛ ሐገር ጋዜጠኞች ብቻ ነው::አዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ እነዚህን ሰዎች ረ/ፕ /ተባባሪ ፕሮፌሰር( እገሌ) ብሎደብዳቤ አይፅፍላቸውም:: ዩንቨርስቲዮቹ ለእነዚህ ሰዎች አቶ (እገሌ) ብሎ ነው ደብዳቤ የሚፅፍላቸው:: ጋዜጠኞች ይህን ስያሜ የሚሰጡት ዶክተር ላልሆነ ሰው ከፍ ማድረጊያ እየመሰላቸው የሚጠሩበት ስያሜ ነው:: ለነገሩ ባይገርማችሁ አሁን ደግሞ እጩ ዶክተር" እየተባለ መጠራት ትጀምሯል:: በማለት ተሰብሳቢውን ፈገግ አድርገውታል::" በማልት የገለፁ ሲሆን አያይዘውም
የክብር ዶክትሬትን በተመለከተ ብቸኛዋና በጥሩ አርአያነት የምትጠቀሰው ጋዜጠኛ ማእዛ ብሩ ናት:: ከባህርዳር ዩንቨርስቲ የክብር ዶክተር ሽልማትን ስትቀበል "በለመደ አፋችሁ ዶክተር ብላችሁ እንዳትጠሩኝ" ብላ የተናገረችውን አድንቀው ተናግረዋል:: እኔም ለፕሮፌሰር ማስረሻ ፕሮግራሙ ካለቀ በኃላ አንድ ጥያቄ አነሳሁላቸው "የዩንቨርሲቲው ሰዎች እኮ ናቸው ጋዜጠኞቹን በረዳት ፕሮፌሰር / በተባባሪ ፕሮፌሰር ስም ጥሩኝ የሚሉት እነሱ እንጂ ጋዜጠኛው አይደለም" ስላቸው በትህትና ወንድሜ "እነዚህ ሰዎች በራሳቸውና ባገኙት እውቀት የማይተማመኑ ሰዎች ናቸው:: እንዲህ የሚሉ ካሉ ያሳዝናሉ" ብለውኛል::
በዚህ ፕሮግራም ላይ የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋን ጨምሮ የኢትዮጵያ በርካታ ምሁራን ተገኝተው ነበር::
ከወዳጄ yitbarer Yetebarek Walelegen ገፅ የተገኘ።