የቦ ታክስ

ለዲያስፓራ አባላት አሁን ኢትዮጵያ ላላችሁ። የአሜሪካ ታክሳችሁን ካላችሁበት ሆናችሁ እንድታሰሩ ነገሮችን ሁሉ አስተካክለናል። ያልተሰራ የታክስ ውዝፍ (Back Tax)፣ መስተካከል ያለበት ታክስ (Amendment), የዚህ አመት ታክስ እና ሌሎችንም እንሰራለን።በViber ሆነ Whatspp ይደውሉልን። 619 255 5530 ። YebboTax info@yebbo.com Yebbo.com

Tuesday, January 4, 2022

Ethiopia is the second country for all Africans," said Senegal's ambassador

"ኢትዮጵያ ለመላው አፍሪካውያን ሁለተኛ ሀገር ናት" ፦የሴኔጋል አምባሳደር 
*******************

ኢትዮጵያ ለመላው አፍሪካውያን ሁለተኛ ሀገር ናት ሲሉ በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙት የሴኔጋል አምባሳደር መሀመድ ላሚን ቲያው ገለጹ።

አምባሳደሩ የሹመት ደብዳቤያቸውን ቅጂ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኘሮቶኮል ጉዳዮች ምክትል ሹም ለሆኑት አምባሳደር ዓለማየሁ ሰውአገኝ አቅርበዋል። 

በወቅቱም ተሿሚ አምባሳደሩ ኢትዮጵያ ለመላው አፍሪካ ሁለተኛ ሀገር መሆኗን ጠቅሰው ÷ ሴኔጋል ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ታሪካዊ የሁለትዮሽ ግንኙነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ፍላጎት መኖሩን  ተናግረዋል። 

በሥራ ቆይታቸውም በሁለቱ ሀገራት መካከል በባሕል እና ቱሪዝም ዘርፎች ያለውን ትብብር ለማስፋት እና በኢንዱስትሪ ፓርክ ዘርፍ ከኢትዮጵያ ልምድ ለመቅሰም እንደሚፈልጉም ጠቁመዋል። 

አምባሳደር ዓለማየሁ በበኩላቸው ÷ ሴኔጋልና ኢትዮጵያ ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን አንስተው ÷ የሁለቱ ሀገራት ህዝቦችም ይበልጥ ተጠቃሚ በሚያደርጉ መስኮች ላይ አተኩረው መሥራት እንደሚገባቸው ገልጸዋል።

አምባሳደሩ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው የሥራ ቆይታ የተሳካ ስራ ማከናወን እንዲችሉ ተገቢው ትብብር እንደሚደርግላቸውም አምባሳደር ዓለማየሁ እንዳረጋገጡላቸው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
"Ethiopia is the second country for all Africans," said Senegal's ambassador
 *******************

 New Ethiopian Ambassador to Ethiopia Mohamed Lamin Tiaw

 The Ambassador presented a copy of his credentials to Ambassador Alemayehu Seguegen, Deputy Chief of Protocol at the Ministry of Foreign Affairs.

 He said Ethiopia is the second largest country in Africa and that Senegal wants to strengthen its historic bilateral relations with Ethiopia.

 He said the two countries would like to expand cooperation between the two countries in the fields of culture and tourism and gain experience in the industrial park sector.

 Ambassador Alemayehu on his part said Senegal and Ethiopia have strong diplomatic relations and the people of the two countries should focus on areas that benefit them the most.

 According to information obtained from the Spokesperson's Office of the Ministry of Foreign Affairs, Ambassador Alemayehu assured them that they will be given the necessary cooperation to enable them to carry out their duties successfully during their stay in Ethiopia.



The five superpowers pledged to prevent a nuclear war

አምስቱ የዓለም ኃያላን አገራት የኒውክሌር ጦርነትን ለመከላከል ቃል ገቡ
 ******************

 አምስቱ የዓለም ኃያላን አገራት የኒውክሌር ጦርነትን ላለማድረግና ለመከላከል የሚያስችል አዲስ ስምምነት ማድረጋቸው ተነገረ።
 አምስቱ የዓለም የኒውክሌር ሃይሎች ቻይና ፣ ፈረንሳይ ፣ ሩሲያ ፣ ብሪታንያ እና አሜሪካ ሰኞ እለት በሰጡት የጋራ መግለጫ የኒውክሌር ጦርነትን ለመከላከል እና የጦር መሳሪያ ውድድርን ለማስወገድ ቃል መግባታቸውን ገልጸዋል።

 የኒውክሌር ጦር መሳሪያ መስፋፋትን ለመከላከል ቃል የገቡት እነዚህ የዓለም ኃያላን መንግሥታት የኒውክሌር ጦርነትን ማሸነፍ እንደማይቻል እና ፈጽሞ መዋጋት እንደሌለበት አረጋግጠናል ሲሉም በመግለጫቸው አክለዋል።

 አምስቱ ፈራሚ ሀገራት የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን የኒውክሌር ሃይል ያለመስፋፋት ስምምነትን ፣ ትጥቅ የማስፈታት እና የጦር መሳሪያ ቁጥጥር አለም አቀፍ ስምምነቶችን አክብረው እንደሚቀጥሉም አስታውቀዋል።

 ፒ አምስት በመባል የሚታወቁት አምስቱ የኒውክሌር መንግስታት በአለም ላይ የአቶሚክ መሳሪያ ያላቸው ብቸኛ ሀገራት አይደሉም።

 ህንድ እና ፓኪስታን ሁለቱም የያዙ ሲሆን እስራኤል የኒውክሌር ጦር መሳሪያ እንዳላት በሰፊው ይታመናል።

 ከዚህ ባለፈም ሰሜን ኮሪያ በርካታ የኒውክሌር መሳሪያዎችን እንደሞከረች ይነገራል።

 በትናትናው ዕለት ይፋ የተደረገው የጋራ መግለጫ ለ 10 ኛ ጊዜ ሊካሄድ ከነበረው የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎችን ያለመስፋፋት ስምምነት ግምገማ በፊት ቀደሞ የተደረገ ሲሆን ይህም በዚህ ወር በኒውዮርክ በሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና መሥሪያ ቤት ሊካሄድ ታቅዶ እንደነበረ አርቲ ዘግቧል።
The five superpowers pledged to prevent a nuclear war
 ******************

 The five world powers are said to have reached a new treaty on nuclear non-proliferation.

 The five world nuclear powers, China, France, Russia, Britain and the United States, said in a joint statement on Monday that they were committed to "preventing nuclear war and eliminating arms race."

 "These superpowers, which have pledged to prevent the spread of nuclear weapons, have proved that nuclear war cannot be won and will never be fought," he said in a statement.

 The five signatory countries will continue to abide by the bilateral and multilateral nuclear non-proliferation treaties, disarmament and arms control agreements.

 The five nuclear powers, known as the P5, are not the only ones in the world with nuclear weapons.

 Both India and Pakistan hold, and Israel is widely believed to have nuclear weapons.

 North Korea has reportedly tested a number of nuclear weapons in the past.

 The joint statement issued ahead of the 10th Nuclear Non-Proliferation Treaty (NPT) review, which was scheduled to take place at the United Nations headquarters in New York this month, Arty reported.

In Benishangul-Gumz, 95 members of the Gumuz community, including 8 bandits, returned to the district center

በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል 8 የሽፍታ አባላትን ጨምሮ 95 የጉሙዝ ማህበረሰብ ክፍሎች ወደ ወረዳ ማዕከል ተመለሱ
****************
በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል በዳንጉር ወረዳ 8 የሽፍታ አባላትን ጨምሮ በህወሓት ተላላኪዎች በሚያደርሱባቸው ጫና ጫካ የገቡ 95 የጉሙዝ ማህበረሰብ ክፍሎች ወደ ወረዳ ማዕከል መመለሳቸው ተገለፀ፡፡

የክልሉ መንግስትና በዞኑ የተቋቋመው ኮማንድ ፖስት ያቀረቡትን የሠላም ጥሪ በመቀበል በዳንጉር ወረዳ በርካታ የጉሙዝ ማህበረሰብ ክፍሎች በተዘጋጀላቸው የወረዳ ማዕከል እየገቡ መሆኑም ተገልጿል፡፡

በዛሬው እለትም 2 የታጠቁ እና ሌሎች 6 የሽፍታ አባላትን ጨምሮ 95 የጉሙዝ ማህበረሰብ ክፍሎች ወደ ወረዳ ማዕከል ገብተዋል ተብሏል፡፡

በመካከላችን በነበረው ጥርጣሬና አለመተማመን ምክንያት የተፈጠረው የፀጥታ ችግር ሁላችንንም ዋጋ አስከፍሎናል ብለዋል አቶ መሰረት ፡፡ 

በተሳሳተ መንገድ እርስ በእርስ የምናደርገው ግጭትና ጦርነት ኪሳራ እንጂ ትርፍ የሌለው በመሆኑ፣ የመንግስትን የሠላም ጥሪ መቀበላቸው አግባብና ትክክለኛ ውሳኔ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ህዝቡ በተሳሳተ አሉ ባልታ ወሬ በመስጋት ለመግባት እየፈራ መሆኑን ገልፀው፣ መንግስት የሠላም ጥሪ የጊዜ ገደቡን በማራዘም ንፁሀን ዜጎች የከፋ ጉዳት እንዳይደርስባቸው ሊሰራ ይገባል ብለዋል አቶ መሰረት፡፡ 

በዳንጉር ወረዳ እስካሁን 249 የጉምዝ ማህበረሰብ ክፍሎች የሠላም ጥሪውን ተቀብለው ወደ ወረዳ ማዕከል ማግባታቸውን ዘገባው አመላክቷል ሲል የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዘግቧል ፡፡

In Benishangul-Gumz, 95 members of the Gumuz community, including 8 bandits, returned to the district center
 ****************
 In Benishangul-Gumz State, 95 members of the Gumuz community, including 8 bandits, have been returned to the Woreda Center under pressure from TPLF members, including 8 gang members.

 It is also stated that a large number of Gumuz community members in Dangur woreda are entering the woreda center prepared by the regional government and the zonal command post.


 As many as 95 members of the Gumuz community, including 2 armed men and six bandits, entered the district center today.

 "The insecurity caused by the suspicion and mistrust among us has cost us all dearly," Meseret said.

 He asserted that his confession had been obtained through torture and that his confession had been obtained through torture.

 He said the people are afraid to enter the country due to rumors that the government is in trouble.

 According to the Benishangul-Gumuz Regional State Communication Affairs Office, 249 members of the Gumz community have so far accepted the call for peace and entered the woreda center.

ሩብ ክፍለ ዘመን እንደዋዛ

ሩብ ክፍለ ዘመን እንደዋዛ 
————————————
              (በጀሚል ይርጋ)

    ታህሣስ 26/ 1985 ዓም የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኤርትራን መገንጠል እውን የሚያደርገውን "ሪፈረንደም" የሚታዘቡ ልዑካንን መላኩ ‘ ጣልቃ ገብነትና የሪፈረንደሙም ሂደት የኢትዮዽያ ህዝብን ከወሳኝነት ያገለለ’ መሆኑን ፣ አዲስ አበባ ለጉብኝት ይገኙ ለነበሩት የወቅቱ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ ቡትሮስ ቡትሮስ ጋሊ ተቃውሞአቸውን ለማሰማት ያካሄዱት በአጭር የተቀጨ ሰላማዊ ሰልፍ፣ ሩብ ክፍለ ዘመን ሆነው – 25 ዓመታት።
   የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አዲስ አበባ እንደሚገቡ በመገናኛ ብዙሃን  ከተነገረበት ታህሳስ 24/ 1985 ምሽትና  በቀጣዩ ቀን ባካሄዱት ስብሰባ ነበር ሰላማዊና ሁከት ያልተመላበት ተቃውሞ ለዋና ፀሀፊው ለማሰማት የወሰኑት። 
      ይሁን እንጂ፣ በውሳኔያቸው መሰረት ሰኞ ታህሳስ 26/1985  ሰላማዊ ሰልፍ ቢወጡም ዋና ፀሀፊው ዘንድ ሳይደርሱ ገና ከዩኒቨርስቲው ቅጥር ግቢ እንደወጡ ነበር የፀጥታ ሀይሎች (ታጣቂዎች) በወሰዱት የኃይል እርምጃ ሰልፉ የተበተነው። በወቅቱ የሰልፉን ሂደትና የመንግስትን እርምጃ እንደ ዘገቡት የነፃ ፕሬሶችና ኢሰመጉ ሪፖርት፣ ዓይነ ስውራንና ሴቶች ተማሪዎችን ጨምሮ ብዙዎች ተገድለዋል። ቆስለዋልም። የፀጥታ ኃይሎቹ ሰልፉን ለመበተን የተጠቀሙባቸው መሳሪያዎች ጥይት፣ ዱላና ጩቤ መሆኑን አክለው ገልፀዋል።
    መንግስትና መንግስታዊ ሚዲያዎች በበኩላቸው፣ ሰላማዊ ሰልፉ ህገ ወጥና ፈቃድ ያልተሰጠው መሆኑን፣ እንዲሁም ሰልፉን ለመበተን በተወሰደው እርምጃም ተስፋሁን ወርቁ የተባለ  አንድ ተማሪ መገደሉንና ጥቂቶችም መቁሰላቸውን አሳውቋል። ይሁን እንጂ ይህን የመንግስት መግለጫና ጉዳቱን የገለፀበት አኃዛዊ መረጃ፣ ኢሰመጉና ሌሎች የውጭ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች፣ የዩኒቨርስቲው ተማሪዎችና የነፃው ፕሬስ፣ እውነታውን ያደበሰበሰ ነው ሲሉ ክፉኛ ነበር የተቹት።
    በተቃውሞውና ተቃውሞውን ተከትሎ በደረሰው ጥፋት ዙሪያም በወቅቱ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተማሪዎች ካውንስል ፕሬዝዳንት የነበረው ጋሻው ካሤ እና ሌሎች የካውንስሉ አመራሮች፣ ከምሁራን ደግሞ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም፣ ዶ/ር በፈቃዱ ደግፌ፣ ዶ/ር መኮንን ቢሻው፣ ዶ/ር እሸቱ ጮሌና ሌሎችም በተለያዩ የግሉ ፕሬስ የህትመት ውጤቶች በቃለ–ምልልስ መልክ ሰፊ አስተያየቶችን ሰጥተውበት ነበር። ቆስለው ሆስፒታል የተኙና በተቃውሞው ተሳታፊ የነበሩትም ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል። እናም የወቅቱ ኹነት ምን ይመስል እንደነበር በሰፊው ለመረዳት ያስችላችሁ ዘንድ እነዚህን መፅሄቶች ፈላልጋችሁ ታነቧቸው ዘንድ እጋብዛችኋለሁ። እግረ መንገዳችሁንም የዚያን ጊዜ ተማሪዎች የተቃውሞ መንፈስና የዘንድሮውን አነፃፅራችሁ ትገመግሙበታላችሁ።
   በበኩሌ የተገነዘብኩት ነገር ቢኖር የያኔዎቹ ተማሪዎች ከሁሉም ብሔሮችና ሃይማኖቶች የተውጣጡ ቢሆኑም እንደ አሁኖቹ በገዛ ወንድሞቻቸው ላይ የሚዘምቱና እርስ በርሳቸው ተሻምቀው የሚገዳደሉ አልነበሩም። ስለ ሀገር ተቆርቁረው፣ ለሀገር የሚሞቱ እንጂ። ክብር ለነርሱ ይሁን !!! 

   (ለተቃውሞው 25ኛ ዓመት መታሰቢያ የተፃፈ)

     –  ታህሣስ 26/ 2010 ዓም
       
                 አዲስ አበባ

West Gondar Zone High Court sentenced three brothers to 18 years in prison each on charges of kidnapping.

ፍርድ ቤቱ ሰው የማገት ወንጀል የፈጸሙ ሶስት ወንድማማቾችን በ18 ዓመት ጽኑ እስራት ቀጣ
*******************

የምዕራብ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሰው የማገት ወንጀል ፈጽመዋል ያላቸውን ሶስት ወንድማማቾች እያንዳንዳቸውን በ18 ዓመት ጽኑ እስራት ቀጣ።

የፍርድ ቤቱ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ አበበ ማስሬ ለኢዜአ እንደገለጹት ወንድማማቾቹ በተከሰሱበት ወንጀል ጥፋተኝነታቸው በማስረጃ በመረጋገጡ የቅጣት ውሳኔ ተላልፎባቸዋል።

“ወንድማማቾቹ በመተማ ወረዳ ህዳር 30 ቀን 2014 ዓም በግምት ምሽት 4 ሰዓት ላይ የማሽላ ምርት ወቅተው አውድማ በመጠበቅ ላይ የነበሩ የ14 ዓመት ታዳጊ ህፃንና አንድ ሌላ ግለሰብ ላይ የእገታ ወንጀል በመፈጸማቸው ቅጣት ተላልፎባቸዋል” ብለዋል።

ለጊዜው ካልተያዙ ግብረ አበሮቻቸው ጋር በመሆን ወንጀሉን የፈፀሙት 1ኛ ተከሳሽ መልኬ መካሻው የጦር መሳሪያ በመያዝ፣ 2ኛ ነጋ መካሻውና 3ኛ ተከሳሽ ታከለ መካሻው የተባሉ ወንድማማቾች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

ግለሰቦቹ ተበዳዮችን እጃቸውን አስረው በጫካ በማቆየትና ለጊዜው 50 ሺህ ብር ከቤተሰቦቻቸው ተቀብለው ለሌላ አጋቾች አሳልፈው መስጠታቸው መረጋገጡን ገልፀዋል።

ከታዳጊ ህፃኑ ጋር የታገተው ግለሰብ ከ3 ቀን ቆይታ በኋላ ታህሳስ 3 ቀን 2014 ዓም በግምት ከሌሊቱ 8:00 ሾልኮ በማምለጥ እራሱን ማዳን እንደቻለ ተናግረዋል።

አጋቾቹ ታዳጊ ህፃኑን ደብቀው ከማሰቃየታቸው በላይ በድጋሜ ከቤተሰቦቹ 160 ሺህ ብር ተቀብለው እንደለቀቁት ማስረጃ መረጋገጡን አብራርተዋል።

ወንድማማቾቹ ወንጀሉን ከፈፀሙ በኋላ ለጊዜው ከአካባቢው ቢሰወሩም ፖሊስ ባደረገባቸው ክትትል ታህሳስ 9 ቀን 2014 ዓ.ም በቁጥጥር ስር ውለው ክስ እንደተመሰረተባቸው ባለሙያው አስረድተዋል።

“አቃቢ ህግ በሰውና በሰነድ ማስረጃ በማስደገፍ በወንድማማቾች ላይ የመሰረተውን ክስ የተመለከተው የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የወንጀል መቅጫ 1995/590 ሐ ተላልፈው በመገኘታቸው ጥፋተኝነታቸውን አረጓግጧል” ብለዋል።

ፍርድ ቤቱ ዛሬ ባስቻለው ችሎት ጥፋተኛ ባላቸው ሶስት ወንድማማቾች ላይ እያንዳንዳቸውን በ18 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ውሳኔ ማሳለፉን ባለሙያው አስታውቀዋል።

እንደ ባለሙያው ገለጻ ፍርድ ቤቱ  በወንጀሉ ተሳትፈዋል የተባሉ ሌሎች ተጠርጣሪዎች ተይዘው ለህግ እንዲቀርቡ ለፖሊስ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
The court sentenced three brothers to 18 years in prison for kidnapping
 *******************

 West Gondar Zone High Court sentenced three brothers to 18 years in prison each on charges of kidnapping.

 The court's public relations expert, Abebe Masre, told ENA that the brothers had been convicted of the charges.

 "The brothers were fined for kidnapping a 14-year-old boy and another person who were waiting for a threshing floor during a sorghum harvest on November 30, 2014 in Metema Woreda," he said.

 He said the first defendant, Melke Mekashaw, and Nega Mekashaw, and the third defendant, Takele Mekashaw, were armed with their accomplices.

 He asserted that his confession had been obtained through torture and that his confession had been obtained through torture.

 The hostage-taker managed to escape by escaping around 8:00 pm on December 3, 2014, after a three-day stay.

 He explained that the abductors not only tortured the child but also took 160,000 birr from his family and released him.

 The brothers disappeared from the area after committing the crime, but were arrested and charged on December 9, 2014, according to the expert.

 "The zonal high court, which heard the prosecution's case against the brothers on the basis of human and documentary evidence, found them guilty of violating the 1995/590C Criminal Code," he said.

 The court sentenced three brothers to 18 years in prison each, the expert said.

 According to the expert, the court ordered the arrest of the other suspects in connection with the crime and brought them to justice.


Diaspora Park inaugurated

የዳያስፖራ ፓርክ ተመረቀ
*********************

የዳያስፖራ ፓርክ በአዲስ አበባ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተመረቀ።

ዳያስፖራዎችም በፓርኩ ዉስጥ የተለያዩ ችግኞችን በመትከል አረንጓዴ አሻራቸዉን አኑረዋል። 

ኦቢኤን ያነጋገርናቸዉ ዳያስፖራዎችም የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብሩ ተሳታፊ በመሆናችን ተደስተናል ብለዋል። 

የፓርኩን ምረቃ ምክንያት በማድረግ ከ4 ሺህ በላይ ችግኞች በዳያስፖራዎቹ ተተክለዋል።

Diaspora Park inaugurated
 *********************

 Diaspora Park inaugurated by Addis Ababa City Administration Mayor Adanech Abebe.

 The Diaspora has also planted green seedlings in the park.

 The Diaspora we spoke to said they were happy to be part of the green fingerprint program.

 As a result of the graduation of the park, more than 4,000 seedlings have been planted in the Diaspora.


ዳያስፖራው የተሳተፈበት የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር እየተካሄደ ነው

ዳያስፖራው የተሳተፈበት የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር እየተካሄደ ነው
******************

የዳያስፖራውን ማህብረሰብ ያሳተፈ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር በአዲስ አበባ ከተማ በመካሄድ ላይ ነው። 

መርሀ ግብሩ በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጀው የዳያስፖራ ፓርክ ውስጥ እየተካሄደ ሲሆን በከንቲባ አዳነች አበቤ መሪነት በርካታ የዳያስፖራ አባላት የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ እያካሄዱ ይገኛሉ።

ከንቲባዋ በመርሀ ግብሩ መክፈቻ ባስተላለፉት መልዕክትም፤  በውጭው ዓለም ኢትዮጵያ ጫና ሲደርስባት ዳያስፖራው አቅሙን ሳይሰስት ትግል ሲያደርግ መቆየቱን ጠቅሰዋል።

ትውልድ እንዲማርና ወቅቱን እንዲያስብ እንዲሁም አካባቢን ለማልማት ለዳያስፖራው መታሠቢያ ይሆን ዘንድ ከተማ አስተዳደሩ የዳያስፖራ ፓርክ ማዘጋጀቱን ተናግረዋል። 

ይህ መታሠቢያ ትርጉሙ ከአረንጓዴ ልማት በላይ ነው። የዳያስፖራው የአረንጓዴ አሻራ ተሳትፎም እንደሚበረታታ እንደሆነ ገልጸዋል።

በመርሀ ግብሩ ተሳትፎ ያደረጉ ዳያስፖራዎች የእናት አገር ጥሪን ተቀብለው አሻራ ለማኖር መብቃታቸው ልዩ ስሜት እንደፈጠረባቸው ገልጸዋል። 

በቀጣይም መሰል ተሳትፎዎችን በማጉላት አገርን በሁሉም መስክ ለመደገፍ ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል ሲል ኢ ፕ ድ ዘግቧል።
A green fingerprint program is underway with the participation of the Diaspora
 ******************

 A green fingerprint transplanting program involving the Diaspora community is underway in Addis Ababa.

 The program is being held at the Diaspora Park in Addis Ababa.

 In a message delivered by the mayor at the opening of the program:  He said the Diaspora has been struggling despite Ethiopia's pressure from the outside world.

 He said the city administration has set up a Diaspora Park as a reminder to the Diaspora to educate the generation and think about the season and to develop the environment.

 This memorial means more than green development.  He said the participation of the Diaspora in the green footprint is also encouraged.

 The Diaspora who participated in the program expressed their special feeling that they were able to accept the call of the motherland and leave their mark.

 He further said that they are ready to support the country in all fields by highlighting such participation.



Education begins in South Wollo Zone, Dessie and Lake Cities

በደቡብ ወሎ ዞን ደሴ እና ሀይቅ ከተሞች ትምህርት ተጀመረ
*********************

በህወሓት የሽብር ቡድን ወረራ ምክንያት በደቡብ ወሎ ዞን ደሴ እና ሀይቅ ከተሞች ከሁለት ወር በላይ ተቋርጦ የቆየው ትምህርት በድጋሚ ተጀምሯል።

በሁለቱም ከተሞች ሙሉ ለሙሉ በሚባል ሁኔታ መደበኛ ትምህርት ተጀምሯል።

የሀይቅ ከተማ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ያሬድ ጌታቸው በአሸባሪው ህውሓት ወረራ ምክንያት ሁለት ወር ከ15 ቀን በኃላ በድጋሜ ትምህርት መጀመሩን ገልፀዋል።

ትምህርት ቤቶቹም ባለው ግብዕት መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደትን እያስቀጠሉ እንደሚገኙም ተናግረዋል።

ከ70% በላይ የሚሆኑ ተማሪዎችም በትምህርት ቤቶች ተገኝተው ትምህርታቸውን እየተከታተሉ እንደሚገኙ ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

Education begins in South Wollo Zone, Dessie and Lake Cities
 *********************

 Education that had been suspended for more than two months in the towns of Dessie and Lake Wollo, South Wollo Zone, has resumed.

 Almost all formal education has begun in both cities.

 Jared Getachew, principal of Lake City High School, said he had resumed school two months and 15 days after the terrorist attack.

 He also said that the schools are continuing their formal teaching and learning process with the help of resources.

 According to the Ministry of Education, more than 70% of the students are still attending school.



Large quantities of wheat and oil were purchased to stabilize market prices

የገበያ ዋጋ ለማረጋጋት ከፍተኛ መጠን ያለው የስንዴና ዘይት ግዢ ተፈጸመ
******************
የተረጋጋ ማክሮ ኢኮኖሚ ከማስፍን አንጻር የዋጋ ግሽበትን የመቆጣጠርና የገበያ ዋጋን የማረጋጋት ፋይዳ ያለው የ4 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴና የ12.5 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ግዢ መፈጸሙን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

የገንዘብ ሚኒስቴርና የተጠሪ ተቋማት የመቶ ቀን እቅድ አፈጻጸም ግምገማ በተካሄደበት ወቅት እንደተገለጸው ባለፉት ጥቅምትና ህዳር ወራት የ4 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ ግዥ  ተፈፅሟል፡፡  

ግዥ ከተፈፀመው ስንዴ ውስጥ አንድ ሚሊዮን ሀምሳ አንድ ሺ አንድ መቶ ስልሳ ኩንታል ስንዴ ወደ ሃገር ውስጥ የገባ ሲሆን ይህም የስንዴ ዋጋ ከፍ እንዳይል የራሱ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ነው የተገለጸው፡፡ 

ቀሪው ስንዴ በተቻለ ፍጥነት ተጓጉዞ ወደ ሀገር ውስጥ አንደሚገባም ታወቋል፡፡
በዚሁ ወቅት የ12.5 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ግዢ ተፈጽሞ ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት በሂደት ላይ መሆኑም ተመልክቷል፡፡

የምግብ ዘይትና ዱቄት ከውጭ በፍራንኮ ቫሉታ (አስመጪዎች በራሳቸው የውጭ ምንዛሪ) እንዲያስገቡ በመደረጉ የሸቀጦች ዋጋ ባለበት እንዲቀጥል ማስቻሉም ተገልጽዋል፡፡

በጥቅምት ወር 2014 ዓ.ም 34.2 በመቶ የነበረ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት በህዳር ወር ወደ 33.0 በመቶ ዝቅ ብሏል ተብሏል። 

የሕዳር 2014 ወርሃዊ የምግብ ዋጋ ግሽበት ካለፈው ጥቅምት 2014 ጋር ሲነጻጸር በ1.8 በመቶ የቀነሰ ሲሆን በተመሳሳይ ጊዜ ውስጥ ምግብ ነክ ያልሆኑ ሸቀጦች የዋጋ ግሽበት 1.0 ከመቶ የጨመረ መሆኑን ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘነው  መረጃው  ያመለክታል፡፡
Large quantities of wheat and oil were purchased to stabilize market prices
 ******************
 The Ministry of Finance said it has procured 4 million quintals of wheat and 12.5 million liters of cooking oil, which is important for controlling inflation and stabilizing market prices.

 According to the Ministry of Finance and its affiliated institutions, 4 million quintals of wheat was procured last October and November.

 Out of the purchased wheat, one million fifty-one thousand one hundred and sixty quintals of wheat was imported, which is said to contribute to the increase in the price of wheat.

 It is learned that the rest of the wheat will be transported as soon as possible.
 Meanwhile, 12.5 million liters of cooking oil has been procured and is in the process of being imported.

 It is also stated that the importation of cooking oil and flour by Franco Valuta (importers on their own foreign exchange) has helped keep commodity prices stable.

 Total inflation fell to 34.0 percent in November 2014 from 34.2 percent in November 2014.

 According to the Ministry of Finance, inflation in non-food items increased by 1.0 percent in November 2014, while food inflation fell by 1.8 percent compared to October 2014.

Monday, January 3, 2022

New Year, New location

ከ20 አመታት የአንድ  ቦታ  ቆይታ  በኋላ  የቦ ወደ አዲሱ ህንፃ  ገብቷል። ለደንበኞቻችን  በቀላሉ  ለመገኘት  ብለን  አሁን  ያለነው  ከትልቅ አውራ ጎዳና  ፊት  ለፊት  ነን። የሳንድያጎ ከተማ  ነዋሪ ከሆኑ  እኛን  ለማኘት  አይቸገሩም። አሁን  ያለነው  ብዙ የከተማ  አውቶቡሶች ፌርማታ  አጠገብ  ስለሆነ  በመኪናም ሆነ  በአውቶቡስ  እኛ ጋር  ለመምጣት  እጅግ  በጣም  ቀላል ነው።  
ታዲያ በዚህ  አመት  አገልግሎታችንን በሰፊው  በመዘርጋት  ከሳንድያጎ  ውጭ  ያሉ  ደንበኞቻችንን  ለማገልገል  ቆርጠን  ተነስተናል። በተለይም  ደግሞ  የታክስ  ደንበኞቻችን  የትም  ግዛት  ቢኖሩ  እነሱን  ለማገልገል  ሁሉንም  ነገር አሟልተን  እንገኛለን።

After 20 years in one location, Yebbo have  moved into the new building.  We are now in front of a highway for easy access to our customers.   It is very easy to come by car or bus to us.
 So this year we are committed to expanding our service to serve our customers outside of San Diego.  In particular, we do everything possible to serve our taxpayers, no matter where they live.






 

The majestic life of the King of Laughter and the world record holder of Belachew Girma is in jeopardy.

የአለም የሳቅ ንጉሱና የጊስቡክ የአለም ሪከርድ ባለቤቱ የበላቸው ግርማ ህይወት አደጋ ላይ ነው እንድረስለት ።

ታዋቂው የአለም የሳቅ ንጉስና የደግነት አንባሣደር፣ በጊነስ ቡክ የተለያዩ የአለም ሪከርዶች ባለቤት የሆነው ማስተር  በላቸው ግርማ ባጋጠመው የጭንቅላት እጢ ሆስፒታል ገብቶ ቀዶ ጥገናውን በተሳካ ሁኔታ ቢያጠናቀቅም አሁንም ቢሆን ህይወቱ አስጊ ደረጃ ላይ ነው። የተሻለ ህክምና ያለበት ሀገር ሄዶ ህክምና ያገኝ ዘንድ ሁላችንም ልንረዳው ይገባል።

ይህ ከከምባታ ምድር የፈለቀው ኩሩ ኢትዮጵያዊ ሀገሩን በአለም መድረክ ላይ ብዙዎች በማይሳካላቸውና ከባድ በሆነው የአለም ድንቃድንቅ ተግባራት በሚመዘገቡበት Guines Book of World ላይ በተደጋጋሚ ሪከርዶችን በመስበርና ስሙን እና ሀገሩን በተደጋጋሚ ሰዓት ያስጠራ ድንቅ ኢትዮጵያዊ ነው።

ሆኖም ግን አሁን በበሽታ ተጠቅቶ የአልጋ ቁራኛ ሆኗል ፤ ስለዚህ ይህን ኩሩ ኢትዮጵያዊ ለመርዳትና ለማገዝ ቅዳሜ ህዳር 5/2013 በSky Light Hotel ከቀኑ 9:00 ሠዓት ጀምሮ  የገቢ ማሰባሰቢያና የኪነ ጥበብ ዝግጅቶች ሊደረግለት በአብርሃም ግዛዉ ኢንተርቴመንት አዘጋጅነት ይካሄዳል።

ስለዚህ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ የምትገኙ ዘመድ አዝማዱ ፣ ጓደኞቹ ፣ አድናቂዎቹ ፣ የመንግስት አካላት ፣ ባለሀብቶች እና ሌሎችም መርዳት የምትፈልጉ ወገናቹን ታግዙና ትረዱት ዘንድ በኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ አካዉንት ቁጥር 1000058068277 ማስተር በላቸዉ ግርማ ብላችሁ መርዳት ትችላላችሁ እሱን ለማግኘት በስልክ ቁጥር 0911244101 ወይም 0912374014 ይደዉሉ::
በአክብሮት እንጠይቃለን።
#ሼር በማድረግ መልዕክቱን ለሁሉም ያድርሱት

The majestic life of the King of Laughter and the world record holder of Belachew Girma is in jeopardy.

 The world-renowned laughter and benevolent ambassador, Guinness Book of World Records, has successfully undergone surgery on a brain tumor, but his life is still in danger.  We all need to help him get to a better country and get treatment.

 Born in Kembata, he is a proud Ethiopian who broke his record in the Guinness Book of World Records, one of the most unsuccessful and difficult events in the world.

 But now he is sick and bedridden;  Therefore, to help and support this proud Ethiopian, a fundraising and arts event will be held at the Sky Light Hotel on Saturday, November 5, 2013 at 9:00 AM hosted by Abraham Gizaw Entertainment.

 Therefore, relatives, friends, admirers, government officials, investors and others who want to help, both at home and abroad, can help him by contacting Oromia Cooperative Bank Account No. 1000058068277.
 We respectfully ask.
 # Share the message with everyone

A second round of repatriation program for Diaspora members from Italy was held in Turin

ከጣሊያን ወደ ሀገር ቤት ለሚገቡ የዳያስፖራ አባላት ሁለተኛ ዙር የሽኝት ፕሮግራም በቶሪኖ ተካሄደ
************************ 

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለዳያስፖራው ያቀረቡትን ግብዣ ተቀብለው በጋራ ወደ ሀገር ቤት ለመግባት በዝግጅት ላይ ለሚገኙ በጣሊያን ቶሪኖ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የሽኝት ፕሮግራም ተደርጓል። 

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት አምባሳደር ደሚቱ ሐምቢሳ ኢትዮጵያ በዓይነት እና በገንዘብ ሀገሩን የሚደግፍ እና አንዳንድ ምዕራባውያን በሀገሩ ላይ ለማድረግ የሚፈልጉትን ጫና እና ጣልቃ-ገብነት በድፍረት የሚታገል ጀግና የዳያስፖራ ኮሚኒቲ አላት ብለዋል። 

ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ ከጊዜያዊ ችግሮቿ ቶሎ ለመላቀቅ አይተኬ ሚና እንዳለው አብራርተዋል። 

“እናንተ ሀገር እና ወገኑን ከዘርፈ ብዙ ተግዳሮት ለመታደግ የምትዘምቱ ዘማቾች ናችሁ፤ ስለሆነም ጉዟችሁ እስከዛሬ ታደርጉት ከነበረው ጉዞ የተለየ መሆን አለበት።” ሲሉም ወደ ሀገር ቤት ለመጓዝ ለተዘጋጁት ወገኖች ተናግረዋል። 

“በምትይዟቸው ሻንጣዎች የድጋፍ ቁሳቁሶችን ቅድሚያ ስጡ፣ ብራችሁ በሕጋዊ መንገድ ብቻ መመንዘሩን አረጋግጡ፣ በጦርነቱ የተጎዱትን ከቤተሰብ እኩል ጎብኙ፣ በአጠቃላይ በሚኖራችሁ ቆይታ እና በምታደርጉት እንቅስቃሴ ለሀገርና ወገን ድጋፍ በሚያስገኝ እንዲሁም የሀገራችንን ገፅታ በሚገነባ መልኩ ይሁን” ሲሉም አደራ ማለታቸውን ሮም ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። 

ዘማች የዳያስፖራ አባላት በበኩላቸው መንግሥት ባቀረበው ጥሪ መሠረት ወደ ሀገር ቤት በመግባት የደረሰውን ጥፋት በአካል በመመልከት በመልሶ ግንባታው የድርሻቸውን ለመወጣት እንደሚሄዱ ገልጸዋል። 

ወደ ሀገር በሚሄዱበት ጊዜም የተለያዩ መድኃኒቶች እና የሕክምና ቁሳቁሶች ይዘው ለመሄድ መዘጋጀታቸውን ነው የገለጹት። 

A second round of repatriation program for Diaspora members from Italy was held in Turin
 ***********************

 A reception was held for Ethiopians and Ethiopians of Ethiopian descent in Turin, Italy, who were preparing to enter the country together in response to Prime Minister Abiy Ahmed's invitation to the Diaspora.

 Ambassador Demitu Hambissa, who was present at the event, said Ethiopia has a heroic Diaspora community that supports the country in kind and financially and boldly fights the pressure and interference of some Westerners in the country.

 He said Ethiopia has an important role to play in getting rid of its temporary problems.

 "You are the ones who are fighting to save the country and its people from many challenges;  So your journey should be different from what you have been doing so far. ”  He told those who were preparing to travel home.

 "Priority should be given to luggage, ensure that your money is spent only legally, visit the victims equally as a family, during your stay and in your activities in a way that is supportive of the country and the country and builds the image of our country," according to the Ethiopian embassy in Rome.

 Campaign members of the Diaspora, for their part, said they would go to the country and play their part in rebuilding the dam at the invitation of the government.

 He also said that they are ready to carry various medicines and medical supplies on their way home.


ዳያስፖራው ለኢትዮጵያ ሕልውና ያደረገው ተጋድሎ ባንዳን ያስደነገጠና የኢትዮጵያውያንን አንድነት በተግባር ያሳየ ነው

ዳያስፖራው ለኢትዮጵያ ሕልውና ያደረገው ተጋድሎ ባንዳን ያስደነገጠና የኢትዮጵያውያንን አንድነት በተግባር ያሳየ ነው - አቶ አወል አርባ
*******************
"ዳያስፖራው ለኢትዮጵያ ሕልውና ያደረገው ተጋድሎ ባንዳና ጠላትን ያስደነገጠና የኢትዮጵያዊያንን አንድነት በተግባር ያሳየ ነው'' ሲሉ የአፋር ክልል ርእሰ መስተዳድር አወል አርባ ተናገሩ፡፡

ዳያስፖራው በአፋር ክልል በአሸባሪው ህወሓት ጉዳት የደረሰባቸውን ግለሰቦችና ተቋማት በመደገፍ ረገድ እያደረገው ላለው አስተዋጽኦም ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በአፋር ክልል ርእሰ መዲና ሰመራ የዳያስፖራ ሲምፖዚየም እየተካሄደ ሲሆን፤ በመድረኩም የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አወል አርባና የሰላም ሚኒስትር ብናልፍ አንዱዓለምን ጨምሮ በርካታ እንግዶች ተሳትፈዋል፡፡

ርእሰ መስተዳደሩ በዚህን ወቅት ዳያስፖራው በኢትዮጵያ ህልውና ዘመቻ አኩሪ ታሪክ መስራቱን ተናግረዋል፡፡

በ "#NoMore" ንቅናቄ ብርቱ ተጋድሎ አድርጋችኋል፤ ጫና ለማድረግ የሚፈልጉ አካላትን ደግሞ አሳፍራችኋል" ሲሉም ነው የተናገሩት፡፡

ንቅናቄው ለባንዳና ጠላት ትልቅ ድንጋጤ የፈጠረና የኢትዮጵያውያንን አንድነት በተግባር ያሳየ ሁነት መሆኑንም ርእሰ መስተዳድሩ አንስተዋል፡፡

አሸባሪው ህወሓት በአማራና አፋር ክልሎች ሚሊዮኖች እንዲፈናቀሉ፤ በርካቶች በጅምላ እንዲጨፈጨፉ፣ ሴቶች እንዲደፈሩ ማድረጉንና በዚህም ኢትዮጵያ ጠልነቱን በተግባር እንዳሳየ ተናግረዋል።

የአፋር ህዝብ በአፋር በኩል ኢትዮጵያን ማፍረስ እንደማይቻል በተግባር ማረጋገጡን አንስተው፤ ኢትዮጵያውያን ለአገራቸው ህልውና ዳግም የአድዋ ተጋድሎ ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡

አፋርን በተለይም "ሚሌን ይዤ መደራደሪያ አደርጋለሁ' ያለው አሸባሪ ቡድኑ፤ የጸጥታ መዋቅሩ ከአፋር ህዝብ ጋር የእግር እሳት ሆኖበት ተመልሷል ብለዋል።

ድሉ በአገር ውስጥና የውጭ ኢትዮጵያውያን ርብርብ እንደተገኘ ሁሉ አሁንም በአገር ግንባታው ሌላ ድል መቀዳጀት ይጠይቀናል ብለዋል።

"ኢትዮጵያን በአፋር በኩል መቼም መንካት እንደማይቻል አረጋግጣለሁ" ያሉት ርእሰ መስተዳድሩ፤ ኢትዮጵያዊነት እንደ ጃኬት የሚወልቅና የሚለበስ እንዳልሆነ ዳያስፖራው በተግባር አሳይቷል ብለዋል።

ዳያስፖራው ከዚህ ቀደም ሲያደርግ ለነበረው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ አመስግነው፣ በቀጣይም በመልሶ ግንባታው አሻራቸውን እንዲያሳርፉ ጠይቀዋል።

ለበርካታ ኢንቬስትመንት አማራጮች በታደለውና የቱሪስት መዳረሻዎች በተቸረው አፋር ክልል ኢንቬስት በማድረግ እንዲሳተፉና አገርና ወገን እንዲጠቅሙ ጥሪ ማቅረባቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

የሰላም ሚኒስትር አቶ ብናልፍ አንዱዓለም በበኩላቸው ኢትዮጵያ የገጠማትን ፈተና እንደወርቅ ተፈትና እያለፈች ነው፤ በዚህም ትውልዱ ደማቅ ታሪክ እየፃፈ ይገኛል ብለዋል።

አሸባሪ ቡድኑ የፈጸመው ጭካኔ የተሞላበት ግፍና ያደረሰው ውድመት የባዕድ አገር ወራሪ እንኳ ይፈፅመዋል ተብሎ የማይገመት መሆኑን ጠቅሰው፤ "ያጋጠመንን ችግር ተጋግዘን ማለፍ አለብን" ነው ያሉት፡፡

ዳያስፖራው ወደ አገር ቤት መምጣቱ ታሪካዊ አጋጣሚ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ ከመምጣታቸው በፊትም በየአገራቱ ከኢትዮጵያ ጎን በመቆም ታሪክ የማይረሳው ታላቅ ጀብድ መፈጸማቸውን ተናግረዋል።

"ወደ አገር ቤት መምጣታችሁ ዜጎቻቸውን እንዲወጡ የሚወተውቱ ጠላቶችን ሀሰተኛ ፕሮፓጋንዳ ያጋለጠና ኢትዮጵያውያንን ያኮራ ነው" ሲሉም ተናግረዋል፡፡

በአፋር ክልል በአካል መገኘታችሁ ለክልሉ መልሶ ግንባታ አሻራ ለማስቀመጥ የምትጀምሩበት አጋጣሚ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሐመድ እድሪስ የዳያስፖራው ማህበረሰብ ተሳትፎ ለአገረ መንግስት ግንባታ ስኬት ወሳኝ ሚና እንዳለው ገልጸዋል፡፡

በመሆኑም ዳያስፖራው በአገሩ ጉዳይ ላይ ቀጣይነት ባለው መልኩ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡

Curated Products for Generation X

https://amzn.to/3VhbwJz GenX Essentials - Curated Products for Generation X ...

Do you need Ethiopian Power of Attorney where your agent can preform several crucial tasks on your behalf? Such as adoption proceedings, buying movable or immovable properties, paying tax, represent you in governmental and public offices and several others tasks with our your physical presence? If your answer is yes get the Ethiopian Power of Attorney or YEBBO now on sale

Shop Amazon