Saturday, March 14, 2026
በሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ከባለፈው ሁለት ሳምንት ወዲህ ግብፅ ውስጥ በገፍ እየታሰሩ መሆኑ ታወቀ
በሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ከባለፈው ሁለት ሳምንት ወዲህ ግብፅ ውስጥ በገፍ እየታሰሩ መሆኑ ታወቀ
Meseret Media
Mar 14
(መሠረት ሚድያ)- ከሁለት ወራት በፊት ጀምሮ በግብፅ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በኃይል ታፍሰው ወደ ተለያዩ እስር ቤቶች ተወስደው እየታጎሩ መሆኑን በካይሮ የሚኖሩ ስደተኛ ዜጎች ለመሠረት ሚዲያ ተናገሩ።
ለስራ እንደወጡ መንገድ ላይ በግብፅ የፀጥታ አካላት የተወሰዱ እናቶች ከጨቅላ ልጆቻቸው ጋር ጭምር ከተለያዩ ሁለት ወር ያለፋቸው ሲሆን የት እንደተወሰዱም ልናውቅ አልቻልንም ይላሉ።
ገና እድሜያቸው ያልደረሱ ታዳጊዎች ሳይቀር ታፍነው ተወስደዋል የሚሉት ስደተኞቹ ሕጋዊ የመኖሪያ ፍቃድ ያላቸው ኢትዮጵያውያንም ጠፍተዋል ሲሉ ለሚዲያችን ተናግረዋል።
በግብፅ የሚገኘው የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን (UNHCR) ቢሮ ስደተኛ መሆናቸውን አረጋግጦ የሰጣቸው መታወቂያ ሳይቀር በፀጥታ ኃይሎች እየተቀደደ ወደ እስር ተወስደዋል ሲሉም አክለዋል።
Photo: File
ቀደም ሲል በዋና ከተማዋ ካይሮ በርከት ያሉ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በንግድ ስራ እና ሰው ቤት ተቀጥረው በመስራት ይተዳደሩ እንደነበር የገለፁት እነዚሁ የመሠረት ሚዲያ ምንጮች በአሁኑ ወቅት ልጆቻቸው ሳይቀር ከትምህርት ገበታቸው ተገልለው በቤት ውስጥ ተዘግተው እንደሚውሉ ነው የተናገሩት።
የኃይል አፈሳ እየተፈፀመ ያለው በኢትዮጵያውያን እና በኤርትራውያን ስደተኞች ላይ ብቻ መሆኑን እና ኤርትራውያን በኤምባሲያቸው አማካኝነት ወደ አገራቸው እየተሸኙ ሲሆን በሺህዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ግን ገና የታሰሩበት አድራሻ እንኳ ማወቅ አልተቻለም ብለዋል።
ይህንኑ አስመልክቶ በግብፅ የኢትዮጵያ ኤምባሲ እንዲጠይቅልን በተደጋጋሚ ብናመለክትም ሰሚ አላገኘንም ሲሉ ተናግረዋል።
-መሠረት ሚድያ-
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
የቦ ታክስ
ለዲያስፓራ አባላት በሙሉ እንዲሁም አሁን ኢትዮጵያ ላላችሁ። የአሜሪካ ታክሳችሁን ካላችሁበት ሆናችሁ እንድታሰሩ ነገሮችን ሁሉ አናስተካክላለናል። ያልተሰራ የታክስ ውዝፍ (Back Tax)፣ መስተካከል ያለበት ታክስ (Amendment) እንችላለን። የዚህ አመት ታክስ እና ሌሎችንም እንሰራለን።በViberም ሆነ Whatspp ይደውሉልን። ስልክ ቁጥራችን 619 255 5530 ነው ። YebboTax info@yebbo.com Yebbo.com
Translate
Do you need Ethiopian Power of Attorney where your agent can preform several crucial tasks on your behalf? Such as adoption proceedings, buying movable or immovable properties, paying tax, represent you in governmental and public offices and several others tasks with our your physical presence? If your answer is yes get the Ethiopian Power of Attorney or YEBBO now on sale
Shop Amazon
Call Yebbo
የቦ ኮሚኒኬሽን ኔት ወርክ ፣
ለ25 አመታት በላይ የስራ ልምድ ያካበተው
የእናንተው በእናንተው።
ከምሰጣቸው አገልግሎቶች ውስጥ
የውክልና አገልግሎት መስጠት
የኢትዮጵያ ፓስፖርት አገልግሎት መስጠት
የቢጫ ካርድ የማውጣት አገልግሎት
የታክስ አገልግሎት መስጠት (የትም የኢትዮጵያ ግዛት ይኑሩ)
የጉዞ ወኪል
የትርጉም ስራ አገልግሎት
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር
619-255-5530 ይደውሉ።
No comments:
Post a Comment
Note: Only a member of this blog may post a comment.