Shop Amazon

Monday, August 18, 2014

Renowned Ethiopian Traditional Singer - Artist Enana Dubale Passed Away at age 34 - የድምጻዊት እናና ዱባለ ዜና እረፍት - የድምጻዊት እናና ዱባለ ዜና እረፍት





Renowned Ethiopian Traditional Singer - Artist Enana Dubale
Passed Away at age 34 - የድምጻዊት እናና ዱባለ ዜና እረፍት - የድምጻዊት እናና ዱባለ ዜና እረፍት
ድምጻዊት እናና ዱባለ በተወለደች 34 ዓመቷ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች
አምስቱ አርጎየዎች በመባል ከአንድ ቤተሰብ የፈለቁ በልዩ ተሰጥኦ የአዚያዚያም ጥበባቸዉ መላዉን የሙዚቃ አድማጭ ካስደመሙት
ድንቅ አርቲስቶች ዉስጥ አንዷ አና ትንሿ ማለትም የመጨረሻ ልጅ የሆነችዉ ምርጥ ድምጻዊት እናና ዱባለ በደረሰባት ድንገተኛ ህመም
ለአንድ ወር ያህል በህክምና ሰትረዳ ቆይታ በትናንትናዉ እለት በተወለደች በሰላሳ አራት አምቷ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
አርቲስት እናና ዱባለ በመጀመሪያዉ ዘፈኗ <ጭር ሲል አልወድም> በሚለዉ ጣዕመ ዜማዋ የመላዉን የኢትዮጵያ አድማጮቿን ቀልብ
በመሳብ ቀጥላም ከአርቲስት አበበ ፍቃዴ ጋር ሁለት አልበም ከመስራቷም ሌላ ለብቻዋ <ኮራ> በሚል የአልበም ስያሜ ባሳተመችዉ
አልበም  ልዩ ተደናቂነትን ያተረፈች ድምጻዊት የነበረች።  ድምጻዊት እናና ዱባለ በህይወት ዘመኗ በጣም ቅን አሳቢ ፣ ሳቂታና ተጫዋች
ነበረች ። አርቲስት እናና ዱባለ በቤተሰቧ ልዩ ፍቅር የሚሰጣት ቤተሰቦቿን አክባሪና የሶስት ወንድ ልጆች እናት ነበርች። 

እኛም የባዉዛ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል የስራ ባልደረቦች በዚች ተወዳጅ ብርቅና ድንቅ አርቲስት ዜና እረፍት የተሰማንን ከባድ ልባዊ ሃዘን
እየገለጽን ለአርቲስት እናና ዱባለ ቤተሰቦችና  ለአድናቂወቿ በሙሉ እግዚያብሔር መጽናናቱን እንዲሰጣቸዉ እንመኛለን። ነፍስ ይማር
 SOURCE

No comments:

Post a Comment