Shop Amazon

Friday, May 1, 2015

ISIS Victmns identified ብርሃኑ ጌታነህ and አያልቅበት ስንታየሁ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 23፣ 2007(ኤፍ.ቢ.ሲ) በቅርቡ በሊቢያ ውስጥ በአሸባሪው አይ ኤስ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉ ኢተዮጵያውያን ማንነት በመለየት ላይ ይገኛል።
በዚህም መሰረት በርካታ የሟች ቤተሰቦች የልጆቻቸውን ሞት ተረድተው ሀዘን ተቀምጠዋል።
ቀደም ብሎ ኢያሱ ይኩኖአምላክ ፣ ባልቻ በለጠ እና ወጣት ብሩክ እና ሌሎች ሁለት ወጣቶች የጨርቆስ አካባቢ ነዋሪዎች የአይ ኤስ ሰለባ መሆናቸው ተለይተው ቤተሰቦቻቸው ሀዘን ላይ መሆናቸው ይታወሳል።

አያልቅበት ስንታየሁ
ጣቢያችን በጎንደር እና ነቀምት ከተሞችም የአሸባሪ ቡድኑ የግፍ ድርጊት ሰለባ የሆኑ ሌሎች ሁለት ቤተሰቦችን አናግሮ መዘገቡ ይታወሳል
አሁን ደግሞ አቧሬ እና ገርጂ አካበቢ ነዋሪ የነበሩ ሌሎች ወጣቶች በአይ ኤስ መገደላቸው ታውቋል።
ወጣቶቹ አያልቅበት ስንታየሁ እና ብርሃኑ ጌታነህ ይባላሉ።
አያልቅበት የ30 አመት ወጣትና ከሶስት አመት በፊት ወደ ሱዳን ያቀና ሲሆን፥ ከእናቱ ጋር ሲኖር የነበረ መሆኑን ከቤተሰቦቹ ተረድተናል።
ብርሃኑ ጌታነህ

አያልቅበት ስንታየሁ ብቸኛ ልጃቸው እንደነበርም እናቱ ተናግረዋል ።
ብርሃኑ ጌታነህ ደግሞ ባለትዳር እና በፎቶግራፉ ላይ እንደምንመለከተው የስምንት እና የአራት አመት ልጆች ያሉት ወጣት ነበር ።
በአዲስ አበባ አቧሬ አካባቢ ይኖር የነበር ሲሆን፥ ከአገር ከወጣ አራት ወር አልፎታል።
ባለቤቱ ብርቱካን ጌቱ ስትባል በአሁኑ ወቅት ባለቤቷን ማጣቷ ተደራራቢ ችግር ላይ እንደጣላት ገልፃለች።
በፍርድ አወቅ አጥቁዬ
ምንጭ፦: ፋና

No comments:

Post a Comment