Call Yebbo

YebboTax Ethiopian Banner
ለአሜሪካ ታክስ ከፋዮች፣ አመታዊ ታክሳችሁን፣ ያልተሰራ የታክስ ውዝፍ (Backtax)፣ መስተካከል ያለበት ታክስ (Amdment) ካላችሁ የትም ሆናችሁ ማሰራት ትችላለችሁ።የኢትዮጵያ ፓስፖርት፣ የቢጫ ካርድ፣ ውክልና፣ የትርጉም ስራ ይፈልጋሉ? በViber/WhatsApp በ619 255 5530 ደውሉልን። info@yebbo.com Yebbo.com

Friday, November 9, 2018

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሶማሊያ አቋርጦት የነበረውን በረራ ከ41 ዓመታት በኋላ ዳግም ጀመረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሶማሊያ አቋርጦት የነበረውን በረራ ከ41 ዓመታት በኋላ ዳግም ጀመረ
********************************************************************************

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ሶማሊያ ላለፉት 41 ዓመታት አቋርጦት  የነበረውን  በረራ ዳግም ጀመረ፡፡

አየር መንገዱ በሶማሊያ በነበረው የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት በረራውን አቋርጦ እንደነበር የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገ/ማርያም አስታውቀዋል፡፡

አየር መንገዱ በአገሪቱ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ሞቃድሾ ይፋዊ በረራ መጀመሩን አስታውቀዋል፡፡

ይህም ለሶማሊያዊያን አየር መንገዱን በመጠቀም  ከቀሪው አለም ጋር ለመገናኘት በር እንደሚከፍትላቸው አመልክተዋል፡፡

ለሶማሊያ መልሶ ግንባታና ለኢትዮጵያና ሶማሊያ ህዝቦች የቀደመ ትስስር መጠናከርም የበረራው መጀመር ፋይዳው የጎላ መሆኑን አቶ ተወልደ ተናግረዋል፡፡

አየር መንገዱ ዳግም በረራ የማስጀመር ስነ ስርዓቱ ዛሬ ማለዳ በቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በይፋ አብስሯል፡፡

በአባይነህ ጥላሁን

No comments:

Post a Comment

Note: Only a member of this blog may post a comment.

Do you need Ethiopian Power of Attorney where your agent can preform several crucial tasks on your behalf? Such as adoption proceedings, buying movable or immovable properties, paying tax, represent you in governmental and public offices and several others tasks with our your physical presence? If your answer is yes get the Ethiopian Power of Attorney or YEBBO now on sale

Shop Amazon