Shop Amazon

Wednesday, November 7, 2018

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በአማራ ክልል ጉብኝት ሊያደርጉ ነው

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በአማራ ክልል ጉብኝት ሊያደርጉ ነው

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 28 ፣ 2011 (ኤፍ ቢ ሲ) የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በአማራ ክልል ጉብኝት ሊያደርጉ ነው።

ፕሬዚዳንቱ ከፊታችን ዓርብ ጀምሮ በጎንደር እና ባህር ዳር ከተሞች ጉብኝት ያደርጋሉ።

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ዓርብ ጎንደር ከተማ የሚገቡ ሲሆን፥ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድን ጨምሮ የአማራ ክልል ከፍተኛ ባለስልጣናት አቀባበል ያደርጉላቸዋል።

በቆይታቸውም በጎንደር እና አካባቢው የሚገኙ ታሪካዊ ቦታዎችን እና የልማት ስራዎችን እንደሚጎበኙ፥ የጎንደር ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ተስፋዬ ሞገስ ተናግረዋል።

የፕሬዚዳንቱ ጉብኝት በሃገር ደረጃ የተጀመረውን ግንኙነት እንደሚያጠናክረው ታምኖበታል።

በጎንደር ከተማ በርካታ ኤርትራውያን በተለያየ ስራ ተሰማርተው ይገኛሉ።

ከዚህ ቀደም በአማራ ክልል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ወርቅሰሙ ማሞ የተመራ የልዑካን ቡድን በአስመራ ጉብኝት ማድረጉ የሚታወስ ነው።

በነብዩ ዮሃንስ

No comments:

Post a Comment