Friday, November 13, 2020

ህወሃት ጊዜው እየመሸበት ሲሄድ የትግራይ ህዝብ ተቆርቋሪ መስሎ ቀርቧል — የትግራይ ተወላጆች (Walta)


ህወሃት ጊዜው እየመሸበት ሲሄድ የትግራይ ህዝብ ተቆርቋሪ መስሎ ቀርቧል — የትግራይ ተወላጆች
----------------------------------------
ህወሃት ጊዜው እየመሸበት ሲሄድ የትግራይ ህዝብ ተቆርቋሪ መስሎ መቅረቡን በአዲስ አበባ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ገለጹ። 
የትግራይ ተወላጆች ለኢዜአ እንደገለጹት ቡድኑ ኢትዮጵያን ለ27 ዓመታት ሲገዛ በአገርና ህዝብ ላይ የፈፀመው ግፍና በደል በርካታ ነው።
በእነዚህ አመታት ለራሱ ህልውና እና አብረውት ለቆሙት ቡድኖች ከመጥቀም ውጭ ለትግራይ ህዝብ “እዚህ ግባ” የሚባል ጥቅም እንዳላስገኘለትም ያምናሉ።
ሆኖም የጥፋት ቡድኑ አሁን ላይ “ጊዜው እየመሸበት” ሲሄድ የትግራይ ህዝብ ተቆርቋሪ መስሎ ለመቅረብ መሞከሩን ገልጸዋል።
የትግራይን ልዩ ሃይልና ሚኒሻ ለነፍሱ ማቆያ ለማድረግ የጥፋት መልእክተኛ ማድረጉ ደግሞ የህወሃትን ፍፁም የሆነ ግለኝነት የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል።
አቶ ሙዑዝ ገብረ ህይወትና ወይዘሮ መሰሉ ረዳ የተባሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች እንዳሉት ህወሃት የትግራይን ህዝብ ሊወክል የማይችል የጥፋት ቡድን ነው።
ቡድኑ በአገር ላይ ክህደት በመፈፀም የሰሜን እዝ የመከላከያ ሰራዊት ላይ የፈፀመው አሳፋሪ ድርጊት መሆኑን ገልጸው የወንጀሉ ተሳታፊ በሆኑ የምክር ቤት አባላት ላይ ያለመከሰስ መብታቸው መነሳቱም ተገቢ መሆኑን ገልጸዋል።
የትግራይ ወጣት ጊዜው የመሸበትን የህወሃት ቡድን በመታገል ለህግ እንዲቀርብ የመከላከያ ሃይሉን እንዲያግዝም ጠይቀዋል።
የህወሃት ጁንታ የራሱን ልጆችና ዘመዶች በተለያዩ የአለም አገራት እያኖረ የድሃውን ህዝብ ልጅ ከትምህርት እያቋረጠ የአገር መከላከያ ሰራዊትን እንዲወጋ ማሰለፉ በወላጆችም ይሁን በወጣቶቹ ተቀባይነት የሌለው መሆኑን ገልጸዋል።
የትግራይ ልዩ ሃይልና ሚኒሻ አባላት ጁንታውን “እምቢ” በማለት እጃቸውን ለአገር መከላከያ ሰራዊት እንዲሰጡም አሳስበዋል።
የህወሃት ጁንታ በህግ ማስከበሩ ሂደት በቁጥጥር ስር ውሎ በጦር ፍርድ ቤት ሊዳኝ ይገባዋልም ነው ያሉት ነዋሪዎቹ።
(ምንጭ፦ ኢዜአ)

No comments:

Post a Comment

Note: Only a member of this blog may post a comment.

የቦ ታክስ

ለዲያስፓራ አባላት በሙሉ እንዲሁም አሁን ኢትዮጵያ ላላችሁ። የአሜሪካ ታክሳችሁን ካላችሁበት ሆናችሁ እንድታሰሩ ነገሮችን ሁሉ አናስተካክላለናል። ያልተሰራ የታክስ ውዝፍ (Back Tax)፣ መስተካከል ያለበት ታክስ (Amendment) እንችላለን። የዚህ አመት ታክስ እና ሌሎችንም እንሰራለን።በViberም ሆነ Whatspp ይደውሉልን። ስልክ ቁጥራችን 619 255 5530 ነው ። YebboTax info@yebbo.com Yebbo.com

Translate

Do you need Ethiopian Power of Attorney where your agent can preform several crucial tasks on your behalf? Such as adoption proceedings, buying movable or immovable properties, paying tax, represent you in governmental and public offices and several others tasks with our your physical presence? If your answer is yes get the Ethiopian Power of Attorney or YEBBO now on sale

Shop Amazon

Call Yebbo

የቦ ኮሚኒኬሽን ኔት ወርክ ፣ ለ25 አመታት በላይ የስራ ልምድ ያካበተው የእናንተው በእናንተው። ከምሰጣቸው አገልግሎቶች ውስጥ የውክልና አገልግሎት መስጠት የኢትዮጵያ ፓስፖርት አገልግሎት መስጠት የቢጫ ካርድ የማውጣት አገልግሎት የታክስ አገልግሎት መስጠት (የትም የኢትዮጵያ ግዛት ይኑሩ) የጉዞ ወኪል የትርጉም ስራ አገልግሎት ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 619-255-5530 ይደውሉ።