የቦ ታክስ

ለዲያስፓራ አባላት አሁን ኢትዮጵያ ላላችሁ። የአሜሪካ ታክሳችሁን ካላችሁበት ሆናችሁ እንድታሰሩ ነገሮችን ሁሉ አስተካክለናል። ያልተሰራ የታክስ ውዝፍ (Back Tax)፣ መስተካከል ያለበት ታክስ (Amendment), የዚህ አመት ታክስ እና ሌሎችንም እንሰራለን።በViber ሆነ Whatspp ይደውሉልን። 619 255 5530 ። YebboTax info@yebbo.com Yebbo.com

Saturday, December 12, 2020

Former Ethiopian Prime Minister Fikret Selassie Wegderes has died at the age of 75

የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ፍቅረሥላሴ ወግደረስ በ75 ዓመታቸው አረፉ 
 
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 3 /2013(ኢዜአ) የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ፍቅረስላሴ ወግደረስ ባጋጠማቸው የልብ ህምም ምክንያት በየረር ሆስፒታል በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ማለዳ በ75 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

ኢዜአ ከቅርብ ወዳጆቻቸው ካገኘው መረጃ ለመረዳት እንደቻለው፤ የቀብር ስነ-ስርዓታችውን የሚያስተባብር ኮሚቴ እንደሚቋቋምና ቀብራቸው የሚፈጸምበት ቀን ወደፊት ይገለጻል።
 
ፍቅረሥላሴ ወግደረስ የተወለዱት ሐምሌ 7 ቀን 1937 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተለምዶ ቀጨኔ ተብሎ በሚጠራው ሰፈር ነው። 
 
በኢትዮጵያ አየር ኃይል ማሰልጠኛ ወጣት ካዴት ሆነው በመግባት በ1955 ዓ.ም የተመረቁ ሲሆን በአሜሪካ አገርም ስልጠና ወስደዋል። 
 
የ1966ቱ የኢትዮጵያ አብዮት ሲፈነዳ አየር ሃይልን ወክለው የጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ አባል እንደነበሩ መረጃዎች ያመለክታሉ። 
 
በተለያዩ የስልጣን እርከኖች አገራቸወን ያገለገሉት ፍቅረሥላሴ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ፓርቲ (ኢሰፓ) አደራጅ ኮሚቴና የደርግ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ነበሩ። 
 
ከጳጉሜን 5 ቀን 1979 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 29 ቀን 1982 ዓ.ም የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን አገልግለዋል።
 
"እኛና አብዮቱ እና እኔና አብዮቱ” በሚል ርዕስ ሁለት መጽሐፍት ጽፈው ለአንባብያን አድርሰዋል።
 
ፍቅረሥላሴ ወግደረስ ጨምሮ 42 የደርግ አመራሮች በ1989 ዓ.ም በግድያ፣ በዘር ማጥፋትና በሰብአዊ መብት ጥሰት ወንጀል የተከሰሱ ሲሆን በ2000 ዓ.ም የፍርድ ሂደቱ ሲጠናቀቅ በተከሰሱበት ወንጀል የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው ነበር።
 
በ2003 ዓ.ም የፍቅረሥላሴንና ሌሎች 23 የደርግ አመራሮች የሞት ቅጣት ተነስቶ በ2004 ዓ.ም ከእስር እንዲፈቱ መደረጉ አይዘነጋም።
 
የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር በስልጣን ላይ በነበሩበት ግዜ በተለይም የኢትዮጵያ ታሪክ ለትውልድ ተሰንዶ እንዲቀመጥ የተለያዩ ጥረቶችን በማድረግ እንደሚታወቁ ይነገራል።
 
ፍቅረስላሴ ወግደረስ የሁለት ሴት እና የአንድ ወንድ ልጅ አባት ነበሩ።
Former Ethiopian Prime Minister Fikret Selassie Wegderes has died at the age of 75

 Addis Ababa: December 12, 2014 (ENA) Former Ethiopian Prime Minister Fikreslassie Wegderes has died at the age of 75 in Addis Ababa after receiving medical treatment for a heart attack.

 According to information obtained by ENA from close friends:  A committee to coordinate their funeral will be established and the date of their funeral will be announced in the future.

 Fikreselassie Wegderes was born on July 7, 1937, in a neighborhood commonly known as Kechene in Addis Ababa.

 He entered the Ethiopian Air Force Training College as a young cadet and graduated in 1955 and has trained in the United States.

 Evidence suggests that he was a member of the Derg on behalf of the Air Force during the 1966 Ethiopian Revolution.

 Fikreslassie, who has served in various capacities in his country, was a member of the Organizing Committee of the Ethiopian Workers' Party (ISPA) and the Derg Central Committee.

 He served as Prime Minister of Ethiopia from September 5, 1979 to October 29, 1982.

 He wrote two books, "We and the Revolution, and I and the Revolution."

 42 Derg leaders, including Fikreselassie Wegderes, were convicted in 1989 of murder, genocide, and human rights abuses, and were sentenced to death in 2000 at the end of the trial.

 In 2003, the death sentence of Fikre Selassie and 23 other Derg leaders was lifted.


No comments:

Post a Comment

Note: Only a member of this blog may post a comment.

Curated Products for Generation X

https://amzn.to/3VhbwJz GenX Essentials - Curated Products for Generation X ...

Do you need Ethiopian Power of Attorney where your agent can preform several crucial tasks on your behalf? Such as adoption proceedings, buying movable or immovable properties, paying tax, represent you in governmental and public offices and several others tasks with our your physical presence? If your answer is yes get the Ethiopian Power of Attorney or YEBBO now on sale

Shop Amazon