Sunday, January 2, 2022

የክልሉን አቅም እና የዜጎችን የመልማት ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓት ሊተለም ይገባል፦ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር)

የክልሉን አቅም እና የዜጎችን የመልማት ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓት ሊተለም ይገባል፦ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) 
************************** 

የክልሉን አቅም እና የዜጎችን የመልማት ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓት ሊተለም እንደሚገባ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) ተናገሩ። 

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የገቢ ንቅናቄ ፍኖተ ካርታ አውደ ጥናት በባህርዳር እየተካሄደ ነው። 

በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) ክልሉ ባለው አቅም፣ እንቅስቃሴ እና በሚጠበቅበት መጠን ግብር ለመሰብሰብ ተግዳሮቶች እንዳሉ አንስተዋል። 

በመሆኑም ገቢዎች ቢሮ ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ በጋራ ያዘጋጁት የግብር አሰባሰብ ፍኖተ ካርታው ይታዩ የነበሩ ችግሮችን መቅረፍ የሚያስችል እንደሚሆን ተስፋቸውን ገልጸዋል። 

የክልሉ ገቢ ከሕዝቡ ቁጥር፣ ከመልማት አቅም እና በጦርነቱ ከገጠመው ውድመት አኳያ ሊሠራ እንደሚገባም አሳስበዋል። 

የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ አማካሪዎች ቡድንም የገቢ አሰባሰብ ችግሮች፣ መፍትሔዎች እና ሊወሰዱ የሚገባቸው እርምጃዎች ላይ ጥናት አቅርበዋል። 

በመድረኩ የክልሉ ርዕሰ መንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኝ፣ የንግዱ ማኅበረሰብ አባላት፣ ምሁራን፣ የግብር አምባሳደሮች እና በዘርፉ የሚሠሩ ተቋማት ተወካዮች ተገኝተዋል። 

በራሔል ፍሬው 


No comments:

Post a Comment

Note: Only a member of this blog may post a comment.

የቦ ታክስ

ለዲያስፓራ አባላት በሙሉ እንዲሁም አሁን ኢትዮጵያ ላላችሁ። የአሜሪካ ታክሳችሁን ካላችሁበት ሆናችሁ እንድታሰሩ ነገሮችን ሁሉ አናስተካክላለናል። ያልተሰራ የታክስ ውዝፍ (Back Tax)፣ መስተካከል ያለበት ታክስ (Amendment) እንችላለን። የዚህ አመት ታክስ እና ሌሎችንም እንሰራለን።በViberም ሆነ Whatspp ይደውሉልን። ስልክ ቁጥራችን 619 255 5530 ነው ። YebboTax info@yebbo.com Yebbo.com

Translate

Do you need Ethiopian Power of Attorney where your agent can preform several crucial tasks on your behalf? Such as adoption proceedings, buying movable or immovable properties, paying tax, represent you in governmental and public offices and several others tasks with our your physical presence? If your answer is yes get the Ethiopian Power of Attorney or YEBBO now on sale

Shop Amazon

Call Yebbo

የቦ ኮሚኒኬሽን ኔት ወርክ ፣ ለ25 አመታት በላይ የስራ ልምድ ያካበተው የእናንተው በእናንተው። ከምሰጣቸው አገልግሎቶች ውስጥ የውክልና አገልግሎት መስጠት የኢትዮጵያ ፓስፖርት አገልግሎት መስጠት የቢጫ ካርድ የማውጣት አገልግሎት የታክስ አገልግሎት መስጠት (የትም የኢትዮጵያ ግዛት ይኑሩ) የጉዞ ወኪል የትርጉም ስራ አገልግሎት ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 619-255-5530 ይደውሉ።