የቦ ታክስ

ለዲያስፓራ አባላት አሁን ኢትዮጵያ ላላችሁ። የአሜሪካ ታክሳችሁን ካላችሁበት ሆናችሁ እንድታሰሩ ነገሮችን ሁሉ አስተካክለናል። ያልተሰራ የታክስ ውዝፍ (Back Tax)፣ መስተካከል ያለበት ታክስ (Amendment), የዚህ አመት ታክስ እና ሌሎችንም እንሰራለን።በViber ሆነ Whatspp ይደውሉልን። 619 255 5530 ። YebboTax info@yebbo.com Yebbo.com

Tuesday, January 26, 2021

App uses Amharic language to translate previously unspoken African stories into audio books: CNN

አማርኛ ቋንቋን በመጠቀም ጭምር ያልተነገሩ ነባር የአፍሪካ ታሪኮችን ወደ ድምፅ መጽሐፍት መቀየር የሚያስችል መተግበሪያ ተሠራ-ሲ.ኤን.ኤን
*******************************

የአፍሪካውያን ያልተነገሩ ነባር ታሪኮችን ወደ ድምፅ መጽሐፍት በመቀየር ወጣቱ ትውልድ ስለ ባሕሉ እና ታሪኩ እንዲያውቅ ለማድረግ በመዝናኛ እና በትምህርት መልኩ  ማቅረብ የሚያስችል መተግበሪያ ተሠራ።

የጋናው ግዙፍ የሶፍት ዌር ኩባንያ ሶፍትትራይብ ባለቤት ሄርማን ቺነሪይ-ሄስ አፍሪካውያን አፈ ታሪኮችን በአዲሱ የድምፅ መጽሐፍ መተግበሪያ ለትውልድ ለማስተላለፍ መነሣቱን ተናግሯል።

ይኸው የአፍሪካውያን ድምፆች (Afrikan Echoes) የተሰኘው መተግበሪያ በመጪው መጋቢት ወር ውስጥ እስካሁን ያልተነገሩ 50 የአፍሪካውያን ነባር ታሪኮችን በዩሩባ፣ አማርኛ እና ስዋሂሊ ቋንቋዎችን ጨምሮ በበርካታ የአፍሪካ ቋንቋዎች ተርጉሞ ይፋ ይደረጋል ተብሏል።

የመተግበሪያው ባለቤት የተዘጋጀው የመተገበሪያ ሥርዓት (ፕላትፎርም) በየትኛውም አኗኗር ደረጃ የሚገኙ ሰዎች ያልተነገሩ ታሪኮቻቸውን በዓለም አቀፍ መድረክ ማድረስ እንደሚያስችላቸው ገልጿል።

በመላው አህጉሪቱ የሚኖሩ አፍሪካውያን የታሪክ ተናጋሪዎች ታሪካቸውን በራሳቸው ቋንቋ በድምፅ በመቅረጽ ለአፍሪካውያን ድምፆች (Afrikan Echoes) መላክ እንደሚያስችልም ተጠቁሟል።

የተላኩ ድምፆች ወደ ስቱዲዮ ገብተው ወደ መተግበሪያው እንዲካተቱ ከመደረጋቸው አስቀድሞ በሶፍትትራይብ ኩባንያው ባለቤት ሄርማን ቺነሪይ-ሄስ አማካኝነት በተቋቋመው የፈጠራ ባለሞያዎች ቡድን እንደሚገመገሙ ተገልጿል።  
     
“አሁን ባለንበት ዓለም ነባር ዕውቀቶች በኤሌክትሮኒክ ድምፅ አማካኝነት መተላለፍ ይችላሉ” ያለው  ሄርማን ቺነሪይ-ሄስ  “በመሆኑም እኛ አፍሪካውያን ነባር ዕውቀቶቻችንን ስልኮቻችን ላይ ለማግኘት እየጣርን ነው” በማለት ለሲኤንኤን ተናግሯል።

አያይዞም፣ “አፍሪካውያን ያልሆኑ ሰዎች የአፍሪካውያንን ታሪኮች በአፍሪካውያን እና በአፍሪካውያን የአነጋገር ዘዬ ሲነገሩ ለማዳመጥ ያስችላቸዋል” ብሏል።

App uses Amharic language to translate previously unspoken African stories into audio books: CNN
 ***********************************

 An application was made to entertain and educate the younger generation about the culture and history by translating untold African stories into audio books.

 Herman Chinnery-Hes, owner of software giant Ghana, said it has set out to pass on African legends to its new audiobook application.

 The Afrikan Echoes app is expected to translate 50 African stories in several African languages, including Yoruba, Amharic and Swahili, in March.

 The owner of the app says that the platform will enable people of all walks of life to share their unspoken stories on a global platform.

 He also suggested that African historians across the continent record their stories in their own language and send them to Afrikan Echoes.

 The audio will be reviewed by a team of innovators set up by software company Herman Chineri-Hess before it can be added to the studio and integrated into the app.

 "In today's world, existing knowledge can be transmitted electronically," said Herman Chineri-Hess.


Sunday, January 24, 2021

Ethiopian Land Tenure and Property Rights Law

የኢትዮጵያ የመሬት ይዞታ እና የቤት ባለቤትነት መብት ህግ

የመሬት ይዞታ መብት እና የቤት ባለቤትነት መብቶች የንብረት መብቶች ሲሆኑ ከማይነቀሳቀሱ የንብረት መብቶች ውስጥ የሚመደቡ ናቸው (የፍ/ህ/ቁ 1030)፡፡ ይህም ሁለቱን መብቶች አንድ የሚያደርጋቸው የመጀመርያው ጉዳይ ነው፡፡ 

 ዜጎች በመሬት ላይ ያላቸው መብት  የመሬት ይዞታ መብት ሲሆን ከሽያጭ በስተቀር በመሬቱ ላይ የመጠቀም፣ የይዞታ መብታቸውን በስጦታ፣ በውርስና በኪራይ ለማስተላለፍ ይችላሉ፡፡ 

በሌላ በኩል የግል የቤት ባለቤትነት መብት ደግሞ ለሁሉም ዜጎች እና ህጋዊ ሰውነት ላላቸው ድርጅቶች በእኩልነት የተሰጠ መብት ሲሆን የቤት ባለንብረት የሆኑ ግለሰቦች ወይም ህጋዊ ሰውነት ያላቸው ድርጅቶች በቤቱ ላይ የመጠቀም፣ በስጦታ ወይም በውርስ የማስተላለፍ፣ የመሸጥ እና በሌላ ማንኛውም መንገድ ንብረቱን ለሌላ ወገን  የማስተላለፍ መብት የሚሰጥ ነው፡፡

የቤት የግል ንብረት ባለቤትነት ባለቤቱ ቤቱን በሽያጭ ማስተላለፍን ጨምሮ ሌሎች የንብረት መብቶችን የሚሰጥ ሰፊ መብት ነው፡፡ እዚህ ላይ ልንመለከተው የሚገባው ጉዳይ አንድ የቤት ባለቤት የሆነ ሰው ሁለት መብቶችን አጣምሮ የያዘ ስለመሆኑ ነው፡፡ የመጀመርያው ቤቱን የገነባበት የመሬት ይዞታ መብቱ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በመሬቱ ላይ የተገነባው ቤት ባለቤትነት መብቶች ናቸው፡፡ እነዚህን ሁለት የንብረት መብቶች ለየብቻ ተነጣጥለው ሊታዩ የሚችሉ ባይሆንም የመሬቱ ባለቤት መንግስት እና ህዝብ ሲሆን የቤቱ ባለቤት ደግሞ ቤቱን የገነባው የመሬት ባለይዞታ ግለሰብ ወይም ድርጅት ነው፡፡  ስለሆነም አንድ የቤት ባለቤት በይዞታ መሬቱ ላይ ቤት ሰርቶ ሲሸጥ ቤቱ እና ቤቱ የተሰራበት ይዞታ ተነጣጥለው ሊታዩ የሚችሉ ባለመሆናቸው (intrinsic element) በመሆናቸው የይዞታ መብቱንም ጭምር በሽያጭ እንዳስተላለፈ ይቆጣራል፡፡ 

የኢትዮጵያ ህዝቦች እና ብሄረሰቦች (አርሶ አደሮች፣ ዘላኖች እና የከተማ ኗሪዎች) በእኩልነት የመሬት ባለቤቶች እንደሆኑ ህገመንግስቱ በማያሻማ ሁኔታ ደንግጓል፡፡ ስለሆነም ሁሉም ዜጋ እኩል የሆነ የመሬት ባለቤትነት እና ተጠቃሚነት መብት ያለው ስለመሆኑ ተረጋግጧል ማለት ነው፡፡ ይህ ከሆነ ደግሞ የመሬት ስሪት በገጠር እና በከተማ በልዩነት ሊታይ የሚችል አይደለም፡፡ በገጠር እና በከተማ የመሬት ስሪት ልዩነት አለው ከተባለም ልዩነቱ መምጣት ያለበት አርሶ አደሩ ወይም ዘላኑ የገጠር የእርሻ መሬትና የግጦሽ መሬት ፍላጎት ያለው መሆኑ ሲሆን የከተማው ነዋሪ ደግሞ የመኖርያ ቤት መስርያ ወይም ለተሰማረበት የንግድ ስራ የሚመጥን የድርጅት ቤት መገንቢያ መሬት የማግኘት ፍላጎት ያላቸው መሆኑ ብቻ ነው፡፡

ስለሆነም ከፍ ሲል እንደገለጽነው ህገመንግስቱ በመርህ ደረጃ መሬት የህዝብ እና የመንግስት ነው ካለ በገጠር ያለውን የእርሻ መሬት እና የግጦሽ መሬት ለአርሶ አደሩ እና ለዘላኑ በነጻ እንዲተላለፍ ከፈቀደ በከተማ ለሚኖረው ነዋሪ እና ነጋዴም የቤት መስርያ ቦታ እና ለንግድ ድርጅቱ የሚያስፈልገውን የመስርያ ቦታ በነጻ ወይም ያለክፍያ ሊያገኝ ይገባው ነበር፡፡ 

እዚህ ላይ በአትኩሮት ልንመለከተው የሚገባው ጉዳይ በአሁኑ ስዓት በሃገራችን በተለይም በከተሞች አካባቢ የኗሪዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እና አዳዲስ ከተሞች ሳይቀር እየተፈጠሩ የመጡበት ጊዜ ላይ የምንገኝ በመሆኑ ከፍተኛ የሆነ የመኖርያ ቤት እጥረት አለ፡፡ ይህንን ችግር በመገንዘብ መንግስት በተለያዩ ጊዚያት የተለያዩ ፖሊሲዎችን እና የከተማ የመሬት ስሪት አዋጆችን በማውጣት ወደስራ ገብቶ የነበር ቢሆነም የመኖርያ ቤት ችግሩን ለመቅረፍ አልቻለም፡፡ መጠለያ የማግኘት መብት ደግሞ መሰረታዊ መብት በመሆኑ በማንኛውም ምክንያት ሊገደብ የሚችል አይደለም፡፡ በመሆኑም ሁሉም ዜጋ በሃገሪቱ ሁሉም ክልሎች ተዘዋውሮ የመስራት እና በሚሰራበት አካባቢ የመኖርያ ቤት መስርሪያ ቦታ የማግኘት መብቱ ሊከበርለት ይገባ ነበር፡፡

ነገር ግን አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ የገጠር ኗሪው አርሶ አደር ወይም ዘላን መሬትን በነጻ የማግኘት እና በዚሁ መሬቱ ላይ የመኖርያ ቤት የመገንባት እና የቤት ባለቤት የመሆን እንዲሁም በመሬቱ ላይ የግብርና ስራዎችን የማከናወን ኢኮነሚያዊ መብቱ የተረጋገጠለት ሲሆን የከተማው ነዋሪ በተቃራኒው ግን መሬትን ለመኖርያ ቤት መስርያም ይሁን ለንግድ ስራው ማካሄጃ የሚያገኘው በክፍያ ነው፡፡ እዚህ ላይ ልብ ሊሉት የሚገባው ጉዳይ የገጠሩ ኗሪ መሬትን በነጻ የሚያገኘው ቢሆነም ከዚህ ይዞታው ሲነሳም መንግስት ወይም የከተማው ነዋሪ ተገቢው ካሳ የሚከፈለው መሆኑ ሲሆን በመሬቱ ላይ እኩል መብት ያለው የከተማው ነዋሪ በገጠር ለሚኖርው ካሳ እንዲከፍል መደረጉ የፍትሃዊነት ጥያቄን ከማስነሳቱ ባሻገር በከተማ የሚኖሩ ዜጎችን በሃገሪቱ ኢኮነሚ እኩል ተጠቃሚ የመሆንን እና ንብረት የማፍራት መብታቸውን የሚገድብ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡ ከዚህም ባሻገር አሁን ያለው የገጠር መሬትን ለማስተዳደር የወጡ አዋጆች በከተማ ገቢ በሚያስገኝ ስራ ላይ የተሰማራ ማንኛውም የከተማ ነዋሪ ስራውን ትቶ አርሶ አደር ስካልሆነ ድረስ የገጠር መሬት ተጠቃሚ መሆን እንደማይችል የሚደነግግ ሲሆን ከዚህ በተቃራኒ በገጠር የመኖርያ ቤት ሰርቶ የቤት ባለቤት የሆነው እና በእርሻ ስራ የሚተዳደረው አርሶ አደር ግን እንደከተማው ኗሪ በከተማ የመኖርያም ይሁን የንግድ ድርጅት መስርያ ቦታን በህግ በተወሰነ ክፍያ በእኩልነት የማግኘት መብቱ ተረጋገጠ ነው።

Ethiopian Land Tenure and Property Rights Act

 Land rights and property rights are property rights and are classified as immovable property rights (Law 1030).  This is the first thing that unites the two rights.

 Citizens' right to land is the right to own land, which can be used for sale, inheritance, inheritance and lease, except for sale.

 Private property ownership, on the other hand, is an equal right for all citizens and legal entities, and gives homeowners or legal entities the right to use, gift or inherit the home, sell it, and transfer the property in any other way.

 Private property ownership is a broad right that gives the owner other property rights, including the sale of the home.  The point is, a homeowner has two rights.  The first is the right to own the land on which the house is built, and the second is the right to own the house built on the land.  Although these two property rights cannot be viewed separately, the landowner is the government and the people, and the landlord is the person or organization that built the house.  Therefore, when a landlord builds a house on the land and sells it, the house and the house are not considered separate (intrinsic element).

Saturday, January 23, 2021

ከመተከል ተፈናቃዮች የተመለመሉ ሚሊሻዎችን በማደራጀት ማኅበረሰቡን ከጥቃት መከላከል የሚያስችል አደረጃጀት እንዲፈጠር ተወስኗል፦ አቶ ደመቀ መኮንን

ከመተከል ተፈናቃዮች የተመለመሉ ሚሊሻዎችን በማደራጀት ማኅበረሰቡን ከጥቃት መከላከል የሚያስችል አደረጃጀት እንዲፈጠር ተወስኗል፦ አቶ ደመቀ መኮንን
********************* 

ከመተከል ከተፈናቀሉ የኅብረተሰብ ክፍሎች የተመለመሉ ሚሊሻዎችን በማደራጀት ማኅበረሰቡን በዘላቂነት ከጥቃት መከላከል የሚያስችል አደረጃጀት እንዲፈጠር መወሰኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ገለጹ። 

አቶ ደመቀ ይህን የገለጹት ከመተከል የተፈናቀሉ እና በቻግኒ ራንች በተባለ መጠለያ ጣቢያ ከተጠለሉ ተጎጂዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ነው። 

የአካባቢውን ሰላም በማረጋገጥ ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸው የመመለስ እና ከማኅበረሰቡ ጋር እርቅ የማካሄድ ሥራ እንደሚሠራም ተናግረዋል። 

መንግሥት በተለያየ ምክንያት ለችግር ለተጋለጡ ዜጎች ቅድሚያ በመስጠት የማቋቋም ሥራ እየሠራ ይገኛል ያሉት አቶ ደመቀ፣ የመተከል ተፈናቃዮችን በዘላቂነት ለማቋቋም ቁርጠኛ መሆኑንም ገልጸዋል። 

በውይይቱ ላይ በቤኒ ሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመተከል ዞን ኮማንድ ፖስት አስተባባሪ ተስፋዬ ቤልጅጌ፣ የኮማንድ ፖስቱ ዋና አስተባባሪ ሌ/ጄ አስራት ዴኔሮ፣ አርቲስት እና አክቲቪስት ታማኝ በየነን ጨምሮ የፌዴራል እና የክልል የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። 

በራሔል ፍሬው
Demeke Mekonnen: It has been decided to organize militias to recruit IDPs from the plant.
 *********************

 Deputy Prime Minister and Minister of Foreign Affairs, Demeke Mekonnen, said it has decided to form a militia to protect the community in a sustainable manner by organizing militias recruited from the displaced communities.

 Demeke made the remarks in an interview with victims displaced from the plantation and sheltered at Chagni Ranch.

 He said efforts will be made to ensure peace in the area, repatriate IDPs and reconcile with the community.

 Demeke said the government is working to rehabilitate the displaced people for various reasons.

 Federal and regional officials, including Tesfaye Beljige, coordinator of the post-zone command post in Beni Shangul Gumuz, Lt. Gen. Asrat Denero, artist and activist Tamagne Beyenen, were present at the meeting.

 By Rachel Fruit

 /


/

Wednesday, January 20, 2021

ኢትዮጵያ በወታደራዊ ኃይል ጥንካሬ ከአፍሪካ 6ኛ ከዓለም 60ኛ ሆነች

በያዝነው የፈረንጆቹ ዓመት በወታደራዊ ኃይል ጥንካሬ ዝርዝር ውስጥ ከገቡት የአፍሪካ አገራት መካከል ኢትዮጵያ የስድስተኛነትን ቦታ ስትይዝ በዓለም 60ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣላች።

የተለያዩ መረጃዎችን መሠረት በማድረግ በየዓመቱ የአገራትን ወታደራዊ ጥንካሬ የሚያሳይ ደረጃን የሚያወጣው 'ግሎባል ፋየር ፓወር' የተባለው ተቋም ለዚህ ዓመት ባወጣው ዝርዝር ውስጥ 35 የአፍሪካ አገራት የተካተቱ ሲሆን ኢትዮጵያ የ6ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።

በደረጃው ሰንጠረዥ መሠረት ግብጽ ከአፍሪካ ቀዳሚዋ ስትሆን፣ በመከተል ደግሞ አልጄሪያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ናይጄሪያ፣ ሞሮኮና ኢትዮጵያ በቅደም ተከተል ተቀምጠዋል። የኢትዮጵያ ጎረቤት ሱዳን ደግሞ በ10ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች

ግሎባል ፋየር ፓወር በዓለም ዙሪያ ካሉ አገራት መካከል ባደረገው የወታደራዊ ጥንካሬ ምዘና፣ ከ50 በላይ መመዘኛዎችን የተጠቀመ ሲሆን በዚህም አገራት ያላቸውን የወታደራዊ ኃይል ጥንካሬ በዝርዝር ይፋ አድርጓል።

ድርጅቱ የ138 አገራት ወታደራዊ ጥንካሬን የመዘነ ሲሆን፣ በዓለም በወታደራዊ ኃይላቸው ኃያላን ተብለው በቀዳሚነት የተቀመጡት አሜሪካ፣ ሩሲያ፣ ቻይና፣ ሕንድ፣ ጃፓንና ደቡብ ኮሪያ ከአንድ አስከ ስድስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል።

በዚህ ዝርዝር ውስጥ ኢትዮጵያ በ60ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠች ሲሆን ግብጽ በ13ኛ ደረጃ፣ ሱዳን ደግሞ በ77ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።

ደረጃውን ያወጣው ግሎባል ፋየር ፓወር የየአገራቱን ወታደራዊ የሰው ኃይል፣ ከታጠቁት መሳሪያዎች ጋር በማቅረብ አነጻጽሮ ነው የዓለም አገራትን ወታደራዊ ኃይል ደረጃን ይፋ ያደረገው።

በያዝነው አዲሱ የፈረንጆች ዓመት በዝርዝሩ ውስጥ የ138 አገራት ወታደራዊ ኃይል የተገመገመ ሲሆን፤ የእያንዳንዱ አገር ወታደራዊ አቋም ከተራዘመ የማጥቃትና የመከላከል ወታደራዊ ዘመቻ አቅም አንጻር በተለያዩ መመዘኛዎች ተግምግሞ ነው በግሎባል ፋየር ፓወር ደረጃ የተሰጠው።

የዓመቱ የአገራት ወታደራዊ አቅም ደረጃ ዝርዝር ሲወጣ፣ የሕዝብ ብዛት፣ የሠራዊት መጠን፣ የታጠቁት መሣሪያ፣ የገንዘብ አቅም፣ የአቅርቦት ብቃትና መልክአ ምድራዊ አቀማመጥን ጨምሮ ከ50 በላይ መመዘኛዎችን ተጠቅሟል ተብሏል።

በዚህ ዓመቱ የአገራት ወታደራዊ አቅም አመላካች ዝርዝር ውስጥ ከ35 የአፍሪካ አገራት 6ኛ፣ ከ138 የዓለም አገራት መካከል ደግሞ በ60ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠችው ኢትዮጵያ፣ ካላት 108 ሚሊዮን ሕዝብ አንድ በመቶው ወይም 162 ሺህ የሚሆነው በሠራዊት አባልነት ታቅፏል ተብሏል።

በሠራዊት ብዛት የኢትዮጵያ ሠራዊት 162 ሺህ ወታደሮች ሲኖሯት፣ 24 ተዋጊ አውሮፕላኖች፣ 8 ተዋጊ ሄሊኮፕተሮች፣ 365 ታንኮች፣ 130 ብረት ለበስ ተሽከርካሪዎች፣ 480 ከባድ መድፎች፣ 180 የሮኬት መተኮሻዎች እንዲሁም 65 ቀላል መድፎች ሲኖሩት የአገሪቱ ዓመታዊ ወታደራዊ በጀት ደግሞ 520 ሚሊዮን ዶላር እንደሆነ ግሎባል ፋየር ፓወር ገልጿል።

ከዚህ አንጻር በአህጉረ አፍሪካ በወታደራዊ ኃይል ቀዳሚ የሆነችው ግብጽ ከ104 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ሲሆን፣ አጠቃላይ የወታደር ብዛቷ ደግሞ 930 ሺህ፣ ታዋጊ አውሮፕላን 250፣ ተዋጊ ሄሊኮፕተር 91፣ ታንኮች 3735፣ ከባድ መድፍ 2200፣ ብረት ለበስ ተሽከርካሪዎች 11ሺህ ሲኖራት፣ 10 ቢሊዮን ዶላር የመከላከያ በጀቷ እንደሆነ የደረጃው ሰንጠረዥ አመልክቷል።

ከ138 አገራት መካከል በ77ኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ሱዳን ከ45 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ሲኖራት፣ አጠቃላይ ያላት ወታደር ብዛት 190 ሺህ ነው። በትጥቅ በኩል 45 ተዋጊ አውሮፕላኖች፣ 43 ተዋጊ ሄሊኮፕተሮች፣ 830 ታንኮች፣ 450 ብረት ለበስ ተሽከርካሪ አላት። የአገሪቱ ዓመታዊ የመከላከያ በጀት 4 ቢሊየን ዶላር ነው።

በአፍሪካ አህጉር ግብጽ በወታደራዊ ኃይል የመጀመሪያውን ደረጃ ስትይዝ፣ ኢትዮጵያ 6ኛ፣ ሱዳን ደግሞ 10ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በዚህ ዝርዝር ውስጥ ከኢትዮጵያ ጎረቤት አገራት መካከል ኬንያ ከአፍሪካ 12ኛ፣ ደቡብ ሱዳን 22ኛ፣ ሶማሊያ ደግሞ 34ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።

በግሎባል ፋየር ፓወር የአገራት ወታደራዊ ጥንካሬ የደረጃ ዝርዝር ውስጥ ከ54ቱ የአፍሪካ አገራት የተካተቱት 35 ብቻ ናቸው። በዚህም ምክንያት በወታደራዊ የጥንካሬ አመላካች የደረጃ ሰንጠረዡ ውስጥ 19 የአፍሪካ አገራት ያልተካተቱ ሲሆን የኢትዮጵያ ጎረቤት የሆኑት ኤርትራና ጂቡቲ በዚህ ውስጥ ካልገቡት መካከል ናቸው።

የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል በተለያዩ የአፍሪካ አገራት ውስጥ፣ በአፍሪካ ሕብረት እና በተባበሩት መንግሥታት ስር የሠላም ማስከበር ተልዕኮን ተቀብሎ በመሰማራት ከሌሎች የአህጉሪቱ አገራት የበለጠ ሚና እንዳለው የሚነገር ሲሆን፤ ለተባበሩት መንግሥታት የሠላም ማስከበር ስራ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ወታደሮችን በማቅረብ ቀዳሚ መሆኑ ይጠቀሳል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ በአገሪቱ ሠራዊት አደረጃጀት ላይ ለውጦች እየተደረጉ መሆናቸው፣ እንዲሁም ሠራዊቱን በሥልጠናና በትጥቅ የማዘመን ሥራ እተካሄደ መሆኑ መገለጹ ይታወቃል።






Monday, January 18, 2021



https://travel.state.gov/content/travel/en/traveladvisories/ea/covid-testing-required-us-entry.html#.YAOhoPZL4Wg.facebook

Wednesday, January 13, 2021

ስዩም መስፍንን እና አባይ ፀሐዬን ጨምሮ የጁንታው ቀንደኛ አመራሮች ተደመሰሱ source EBC

ሰበር ዜና
ስዩም መስፍንን እና አባይ ፀሐዬን ጨምሮ የጁንታው ቀንደኛ አመራሮች ተደመሰሱ
**************************

የመከላከያ ሰራዊት ሀይል ስምሪት መምሪያ ሀላፊ ብርጋደል ጀነራል ተስፋዬ አያሌው፣ ጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና ሌሎች የፌዴራል የፀጥታ ተቋማት ዛሬም እንደ ትናንቱ አስደናቂ ጀግንነታቸውን በአንፀባራቂ ድል ታጅበው በድል መወጣት መቀጠላቸውን ለኢዜአ ገልፀዋል።

አሁንም የተቀሩትን የጁንታ አመራሮች የገቡበት ገብተው የማደን ተግባራቸውን አጠናክረው ቀጥለዋልም ብለዋል።

የጁንታው ቡድን ከትጥቅ ትግሉ ጀምሮ በስልጣን ላይ እያለ ኢትዮዽያዊ፣ ከስልጣን ሲወርድና የማይመች ሁኔታ ሲፈጠር ደግሞ አገርን የመበታተንና የማተራመስ ስትራቴጂ ነድፎ የማያሸንፈውንና የማይወጣውን ውጊያ በአባት አርበኝነት ለመፈፀም ሲንቀሳቀስ እንደቆየ ጠቁመዋል። 

ከዚህ ተግባሩ ሊቆጠብም ሆነ ከትላንት ሊማር ያልቻለው የጁንታው ቡድን በሰራዊታችን ላይ ውጊያ ከፍቶ በለኮሰው እሳት በመለብለብ ላይ እንደሚገኝም አረጋግጠዋል።

የጁንታው ቡድን አመራሮች ባለፈው ጥቅምት መጨረሻ በመቀሌ በተካሄደው ዘመቻና ድምሰሳ ወቅት በ48 ሰዓት እጅ እንዲሰጡ ቢለመኑም፣ በማናለብኝነትና ትዕቢተኝነት እምቢ በማለት ወደ ጫካ መግባታቸውን ብርጋዴል ጀነራል ተስፋዬ አስታውሰዋል።

በድጋሚም የአገር መከላከያ ሰራዊት የሀገር ሽማግሌ ጭምር በመላክ እጅ እንዲሰጡ፣ ትጥቅ እንዲፈቱና ጉዳዩቸው በህግ እንዲታይ ቢያስጠይቅም አሻፈረኝ ብለውና የያዙትን የጥበቃ ሀይል በመተማመን እንዲሁም “ተመልሰን እንነሳለን” በሚል የድሮ ብሂል ተሳስተው ያለ እድሜያቸው በዱር በገደሉ ተሸሽገዋል ብለዋል፤ ዋሻዎችን በመጠቀምም ከጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊታችን እይታ ውጪ ለመሆን ጥረት በማድረግ ላይ ናቸው ሲሉም ገልፀዋል።

ሆኖም ደከመኝ ሰለቸኝ የማይለው ጀግናዊ የሀገር መከላከያ ሰራዊትና ሌሎች የፌዴራል የፀጥታ ሀይሎች በዛሬው እለት በጋራ ባደረጉት ጠንካራ ፍተሻ በተከዜ ወንዝ ዳርቻ ቀደም ሲል ሰራዊቱን በማስመታት ኢትዮጵያን ለማተራመስ ሲንቀሳቀሱ፣ ሲያቅዱና ሲመሩ የነበሩ ቀንደኛ የጁንታው አመራሮች ከጥበቃ ሀይላቸው ጋር በነበረው ተኩስ ልውውጥ በውጊያ ላይ ከነጥበቃዎቻቸውና የጥበቃ ወታደራዊ አራሮቻቸው ጋር መደምሰሳቸውን ለኢዜአ ገልፀዋል።

እነዚሁ በነበረው ውጊያ ከጥበቃዎቻቸው ጋር አብረው የተደመሰሱ የጁንታው አመራሮች፣

1. አቶ ስዩም መስፍን፣ የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩ እንዲሁም ውጊያውን የመሩና ሰራዊቱ ከቦታ ቦታ እንዳይንቀሳቀስ ያዘዙ፣ በመጨረሻም በሰራዊቱ ላይ ውጊያ እንዲከፈት ትዕዛዝ የሰጡ፣

2. አቶ አስመላሽ ወልደስላሴ፣ የጁንታው ከፍተኛ የፖለቲካ አመራር የነበሩ

3. አቶ አባይ ፀሃዬ፣ የጁንታው ከፍተኛ የፖለቲካ አመራር የነበሩ

4. ኮሎኔል ኪሮስ ሀጎስ ከመከላከያ የከዳ ከነጥበቃዎቻቸው ተደምስሰዋል

በሌላ በኩል በቁጥጥር ስር የዋሉ ወታደራዊና የክልል አመራሮች
1.  ኮሎኔል ገብረመስቀል ገብረ ኪዳን፣ ከመከላከያ የከዳ
2.  ኮሎኔል ፍስሃ ብርሃኔ፣ ከመከላከያ የከዳ፣
3.  ኮሎኔል ዘረአብሩክ ታደሰ፣ ከመከላከያ የከዳ፣
4.  ኮማንደር ገብረኪዳን አስገዶም የልዩ ሀይል ክፍለ ጦር አዛዥ የነበረ
5.  አቶ መብራህቶም ክንዴ ሀይሉ፣ የክልሉ ውሃ ስራዎች ድርጅት ፋይናንስ ሀላፊ የነበረ በቁጥጥር ስር ውለዋል።
የመከላከያ ሰራዊት ኃይል ስምሪት መምሪያ ሀላፊ ብርጋደል ጀነራል ተስፋዬ አያሌው፣ ባስተላለፉት መልዕክት፣ አሁንም በየዋሻው የተደበቁ የጁንታው ቡድን አባላት በሰላማዊ መንገድ እጅ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። 
“ትርጉም ለሌለው ጁንታ ጠባቂ በመሆን ውድ ህይወታቸውን አትገብሩ፣ ከቻላችሁ ይዛችኋቸው፣ ካልቻላችሁ በሰላም ለሰራዊቱ እጅ እንድትሰጡ ጥሪ አቀርባለሁ” ብለዋል። 
በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ አንዳንድ የትግራይ ተወላጆች ጁንታው ተመልሶ ይመጣል በሚል ያላቸው ግምት የተሳሳተና የጁንታው ቡድን ዘመን ያከተመ መሆኑን አውቀው፣ ከሀገራቸውና ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ ሽግግር መንግስት ጎን በመሆን ትግራይን እንዲያደራጁ፣ እንዲያለሙና መላው ህዝብም የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/EBCworld/
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/EBCNEWSNOW
በምስል የሚገኙ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የኢንስታግራም ገፃችንን ይከተሉ 
https://www.instagram.com/ebcnews1/
አጫጭርና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት የትዊተር ገፃችንን ይከተሉ 
https://twitter.com/ebczena

Monday, January 11, 2021

All The Members Of Congress Who Have Tested Positive For COVID-19

 

All The Members Of Congress Who Have Tested Positive For COVID-19

Here’s a running list of all the lawmakers who have tested positive (or been diagnosed with a presumed infection) and when they announced it. This list will be updated if and when more cases are reported.

1) Rep. Mario Diaz-Balart (R-Fla.) ― March 18 

2) Rep. Ben McAdams (D-Utah) ― March 18

3) Rep. Joe Cunningham (D-S.C.) ― March 19

4) Sen. Rand Paul (R-Ky.) ― March 22

5) Rep. Mike Kelly (R-Pa.) ― March 27

6) Rep. Nydia Velazquez (D-N.Y.) ― March 30

7) Rep. Neal Dunn (R-Fla.) ― April 9

8) Rep. Tom Rice (R-S.C.) ― June 15 

9) Rep. Morgan Griffith (R-Va.) ― July 14

10) Rep. Louie Gohmert (R-Texas) ― July 29

11) Rep. Raul Grijalva (D-Ariz.) ― Aug. 1

12) Rep. Rodney Davis (R-Ill.) ― Aug. 5

13) Sen. Bill Cassidy (R-La.) ― Aug. 20

14) Rep. Dan Meuser (R-Pa.) ― Aug. 22 

15) Rep. Jenniffer González-Colón (R-P.R.) ― Aug. 25

16) Rep. Jahana Hayes (D-Conn.) ― Sept. 20

17) Sen. Mike Lee (R-Utah) ― Oct. 2

18) Sen. Thom Tillis (R-N.C.) ― Oct. 2

19) Sen. Ron Johnson (R-Wis.) ― Oct. 3

20) Rep. Salud Carbajal (D-Calif.) ― Oct. 6

21) Rep. Mike Bost (R-Ill.) ― Oct. 9

22) Rep. Bill Huizenga (R-Mich.) ― Oct. 14

23) Rep. Drew Ferguson (R-Ga.) ― Oct. 30

24) Rep. Michael Waltz (R-Fla.) ― Nov. 9

25) Rep. Don Young (R-Alaska) ― Nov. 12

26) Rep. Cheri Bustos (D-Ill.) ― Nov. 16

27) Rep. Tim Walberg (R-Mich.) ― Nov. 16

28) Sen. Chuck Grassley (R-Iowa) ― Nov. 17

29) Rep. Ed Perlmutter (D-Colo.) ― Nov. 17

30) Rep. Dan Newhouse (R-Wash.) ― Nov. 18

31) Rep. Doug Lamborn (R-Colo.) ― Nov. 18

32) Sen. Rick Scott (R-Fla.) ― Nov. 20

33) Sen. Kelly Loeffler (R-Ga.) ― Nov. 21

34) Rep. Bryan Steil (R-Wis.) ― Nov. 22

35) Rep. Joe Courtney (D-Conn.) ― Nov. 22

36) Rep. Virginia Foxx (R-N.C.) ― Nov. 23

37) Rep. Rick Allen (R-Ga.) ― Nov. 24 

38) Rep. Susie Lee (D-Nev.) ― Nov. 25

39) Rep. Ken Calvert (R-Calif.) ― Nov. 30

40) Rep. Austin Scott (R-Ga.) ― Nov. 30

41) Rep. Ted Budd (R-N.C.) ― Dec. 1

42) Rep. Robert Aderholt (R-Ala.) ― Dec. 4

43) Rep. Barry Loudermilk (R-Ga.) ― Dec. 15

44) Rep. Joe Wilson (R-S.C.) ― Dec. 16

45) Rep. Mike Rogers (R-Ala.) ― Dec. 17

46) Rep. Cedric Richmond (D-La.) ― Dec. 17

47) Rep. Rick Larsen (D-Wash.) ― Dec. 23

48) Rep. Gwen Moore (D-Wis.) ― Dec. 28

49) Rep. Kay Granger (R-Texas) ― Jan. 4

MORE

check

Do you need Ethiopian Power of Attorney where your agent can preform several crucial tasks on your behalf? Such as adoption proceedings, buying movable or immovable properties, paying tax, represent you in governmental and public offices and several others tasks with our your physical presence? If your answer is yes get the Ethiopian Power of Attorney or YEBBO now on sale

Shop Amazon