A Yebbo Global Information Hub

EthioVibes Global

World travel, documents, money, auto, food, culture, history, sports, diaspora, business and technology.

Advertisement

በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የተመራ የልዑካን ቡድን ናይሮቢ ገባ።

Published




በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የተመራ የልዑካን ቡድን ናይሮቢ ገባ።

ህግ የማስከበሩ ዘመቻ የውስጥ ጉዳያችንን በራሳችን አቅም መልክ ለማስያዝ የሚካሄድ በመሆኑና "አክራሪው ሃይል" በህግ ስር ከመሆኑ በፊት ምንም አይነት የውጭ ሃይል እንቅስቃሴ ስርዓት አልበኝነትን በማንገስ የሀገራችንን ሰላም የማደፍረስ ውጤት የሚያስከትል መሆኑን መንግስት አቋሙን ግልፅ አድርጓል።

ይህንኑ አቋም በማስረዳት የቀጠናው አገራት መንግስት የጀመረውን ህግና ህገ መንግስት የማጽናት ጥረት እንዲደግፉ ለማስቻል የጠቅላይ ሚኒስትሩን መልዕክት የያዘና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የተመራ የልዑካን ቡድን ከኬንያው ፕሬዝደንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል።

ምንጭ: በናይሮቢ የኢትዮጵያ ኤምባሲ

#Ethiopia #Ethiopian #kenya

Comments