A Yebbo Global Information Hub

EthioVibes Global

World travel, documents, money, auto, food, culture, history, sports, diaspora, business and technology.

Passport Photo Translation Notary Tax Travel ለኢትዮጵያውያን
Advertisement

የእስራኤል ጦር ኃይል ለሁለት ሳምንታት ያህል በጋዛው አል-ሺፋ ሆስፒታል ላይ ወረራ ካካሄደ በኋላ አብዛኛውን የህክምና ተቋሙን ክፍል ለቆ መውጣቱ ተገለጸ።

Published

 የእስራኤል ጦር ኃይል ለሁለት ሳምንታት ያህል በጋዛው አል-ሺፋ ሆስፒታል ላይ ወረራ ካካሄደ በኋላ አብዛኛውን የህክምና ተቋሙን ክፍል ለቆ መውጣቱ ተገለጸ።

በሆስፒታሉ ላይ ከተካሄደው ወረራ እና ጥቃት በኋላ የጋዛው ሆስፒታል ሕንፃ አፅሙ ቀርቶ ታይቷል።
የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት እንደገለጸው ወታደሮቹ በመቶዎች የሚቆጠሩ “ሽብርተኞችን” ገድለዋል እንዲሁም በቁጥጥር ሥር አውለዋል።
ሠራዊቱ “በሆስፒታሉ ዙሪያ” የጦር መሣሪያዎች እና የደኅንነት መረጃዎች ማግኘቱን ገልጧል።
በሐማስ የሚመራው የጋዛ ጤና ሚኒስቴር በርካታ ሬሳዎችን ጥሎ ለመሄድ መገገዱን አሳውቋል። የአካባቢው ሰዎች ደግሞ ሥፍራው መውደሙን ይናገራሉ።
የእስራኤል ጦር፤ በአል-ሺፋ ሆስፒታል ላይ ወረራ እና ጥቃት የፈጸመው ሐማስ መልሶ ስለተደራጀበት መሆኑን ይገልጣል።
በእስራኤል አየር ድብደባው ምክንያት በሆስፒታሉ ዙሪያ ያሉ ሕንፃዎችንም ጭምር ያጠቃ ነበር። የእስራኤል ጦር የሆስፒታሉን የሕክምና ክፍሎች ያወደምኩት ሐማስ እና የፍልስጤም ኢስላሚክ ጂሀድ ስለሚጠቀሙበት ነው የሚል መግለጫ አውጥቷል።

Comments