Shop Amazon

Tuesday, April 22, 2014

መረዋው ድምፄን ሀኪሞች ለፈውስ ተጠቀሙበት::ተመስገን ማለት ይህን ነው።

Love of Songs
መረዋው ድምፄ ሀኪሞች ለፈውስ ተጠቀሙበት
ጓደኞቼ እንደነገሩኝ ድምጼ እንኳን ለዘፈን ለልቅሶም አይሆን ብለውኝ በቃ ሰው ፊት እንኳን ልዘፍን የሌላ ሙዚቃ ማንጎራጎር አቁሜ ነበር።  አንድ ቀን ግን ከኒዎርክ ከተማ ስልክ ተደወለልኝ። እንድዘፍን ወይም ዘፋኝ እንድፈልግ። በነፃ! ዘፋኝ ፍለጋ ለመሄድ አስቤ ግን በነፃ ማንም እንደማይዝፍን ሰላዎቅሁ አፌን አላበላሽም ብዬ ቁጭ አልሁ። ከዚያ ስልኬ መጮሁ አላቋርጥ አለ። ነገሩ እንዲህ ነው። አንድ ኢትዮጵያዊት ህጻን ታማ ኒዎክ ህክምና ላይ ነበረች (ካንሰር ነው ያመማት) ታዲያ ካለባት ህመም ትንሽ እንኳ ፈገግ እንድትል ታስቦ በእሷ ስም ነበር ዘፈኑን ለመዝፍን የተጥየቅሁት ከዚያ ምራጫ ሳጣ እራሴ ዘፈንሁታ። ብታምኑም ባታምኑም ዘፍኛለሁ። አርቲስት ግን ለመባል ገና አልወሰንሁም::ታዲያ ከዚህ የበለጠ ዘፋኝ ከሄት ይምጣ።

No comments:

Post a Comment