Sunday, May 24, 2015

የተወዳዳሪ ፓርቲዎች የምርጫ አስተያየት

የተወዳዳሪ ፓርቲዎች የምርጫ አስተያየት

ዛሬ ድምፃቸውን ለመስጠት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች የሄዱ በርካታ ኢትዮጵያውያን እንደገለፁልን፤ ድምፃቸውን በሰላማዊ መንገድ መስጠት ችለዋል። ሆኖም አንዳንድ የተቃዋሚ ፓርቲ ተጠሪዎች እንደገለፁልን ግን የተቃዋሚ እጩዎቹ በሚሳተፉበት የምርጫ ጣቢያዎች በታዛቢነት በመደቧቸው ሰዎች ላይ ጫና ሲደረግ ተስተውሏል።
የሰማያዊ ፓርቲ ምክትክ ሊቀመንበር እና የምርጫ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ስለሺ ፈይሳ የዛሬውን ምርጫ አስመልክቶ ሰማያዊ ፓርቲ በተወዳደረበት ቦታ ሁሉ ፤ የምርጫ ታዛቢዎቹን መልምሎ ቢመድብም ፤ ታዛቢዎቹ ከፍተኛ ጫና እንደገጠማቸው ገልፀውልናል።
ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ፤ ዶ/ር መራራ ጉዲና የትውልድ ቦታቸው ከሆነው የአምቦ ከተማ ሆነው የታዘቡትን እንዲህ ሲሉ ለዶይቸ ቬሎ ገልፀዋል።
የመኢአድ ፓርቲ ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሐሪ ደግሞ ምርጫውን ሁለት ቦታ ከፍለው ነው የሚመለከቱት። በአዲስ አበባ እና በክፍለ ሀገር ደረጃ ብለው።
ገዢው ፓርቲ ኢሀዲግ የዛሬውን ምርጫ እንዴት እንደገመገመው ለመጠየቅ የኢህአዴግ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት የህዝብና የውጭ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ደስታ ተስፋውን ለማግኘት በተደጋጋሚ ያደረግነው የስልክ ጥሪ፤ ስብሰባ ላይ እንደሆኑ ተነግሮን ምላሽ ሳናገኝ ቀርተናል። እንዲሁ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር ፤ አቶ ሬድዋን ሁሴን መልሰን እንድንደውል በቀጠሩን ጊዜ ስልኩን ሳያነሱት በመቅረታቸው፤ ከመንግሥት በኩል እንዲሁ አስተያየት ሳናገኝ ቀርተናል።
ልደት አበበ
አርያም ተክሌ

No comments:

Post a Comment

Note: Only a member of this blog may post a comment.

Do you need Ethiopian Power of Attorney where your agent can preform several crucial tasks on your behalf? Such as adoption proceedings, buying movable or immovable properties, paying tax, represent you in governmental and public offices and several others tasks with our your physical presence? If your answer is yes get the Ethiopian Power of Attorney or YEBBO now on sale

Shop Amazon