Shop Amazon

Sunday, October 28, 2018

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የመጀመርያ የአውሮፓ ጉብኝታቸውን በፈረንሳይ ለመጀመር ነገ ወደ ፓሪስ ያቀናሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የመጀመርያ የአውሮፓ ጉብኝታቸውን በፈረንሳይ ለመጀመር ነገ ወደ ፓሪስ ያቀናሉ።
*******************************************************************ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፈረንሳይ ቆይታቸው ከፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር የሁለቱን ሀገራት የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ይመክራሉ።

የፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ በኢትዮጵያ ተሳትፎውን እንዲያሳድግ እንዲሁም በፈረንሳይ ያለውን ቅርስን የመጠበቅና የመንከባከብ ክህሎት የኢትዮጵያ ቅርሶችን ለመታደግ መዋል በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ይወያያሉ።

ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ወደ ፈረንሳይ ያቀኑት ኢማኑኤል ማክሮን ከወራት በፊት ያቀረቡላቸውን ግብዣ ተከትሎ ነው።

ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ ከፓሪስ ቆይታ በኋለ ወደ ጀርመን በርሊን በማቅናት  የቡድን 20 አባል ሀገራት በሚያዘጋጁትና በአፍሪካ ጉዳይ ላይ በሚመክረው ኮምፓክት አፍሪካ ጉበኤ ላይ ይሳተፋሉ።

በጀርመን አነሳሽነት የተቋቋመው ይህ የአፍሪካ የልማት ድጋፍ መርሐግብር ኢትዮጵያን ጨምሮ ሰባት የአፍሪካ ሀገራትን ማዕከል ያደረገ ነው።

ጠቅላይ ሚንስትሩ በጀርመን ቆይታቸው ከመራሂተ መንግስት አንጌላ ሜርክል ጋር ተገናኝተው የሁለቱን ሀገራት የልማት ትብብር የበለጠ ለማጠናካር በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ይወየያሉ።

ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ከ2018 እስከ 2020 የሚቆይ የ213 ሚሊዮን ዩሮ የልማት ትብብር በቅርቡ መፈራረሟ ይታወሳል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ፍራንክ ፈርት በማምራትም አንድ ሆነን አንነሳ ነገን እንገባ በሚል መርህ በተዘጋጀው የኢትዮጵያውያን መድረክ ላይም ይገኛሉ።

በዚህ መድረክ ከ20ሺ በላይ ከመላው አውሮፓ የተውጣጡ ኢትየጵያውያን ከጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ጋር ይወያያሉ በሀገራቸው ሁለንተናዊ ልማት ላይ በሚሳተፉበት መንገድ ላይም ይመክራሉ  ።

በብሩክ ያሬድ

No comments:

Post a Comment