Shop Amazon

Monday, October 29, 2018

ኮ/ል ጎሹ ወልዴ አዲስ አበባ ገቡ

ኮ/ል ጎሹ ወልዴ አዲስ አበባ ገቡ
**********************************
በደርግ ዘመነ መንግስት የአገራችን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና የትምርት ሚኒስትር የነበሩት ኮ/ል ጎሹ ወልዴ ዛሬ አዲሰ አበባ የገቡ ሲሆን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሂሩት ዘመነና እና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአሜሪካ ጉዳዮች ዳ/ጀነራል አቶ ነብያት ጌታቸውን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች አቀባበል አድርግውላቸዋል።

የቀድሞው ሚኒስትር በቦሌ ዓለምአቀፍ አየር መንገድ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የደርግን አገዛዝ በመቃወም ሃላፊነታቸውን በፈቃዳቸው ከለቀቁና ኑሯቸውን በአሜሪካ ካደረጉ ጀምሮ ላለፉት 32 አመታት የአገራቸውን መሬት ሲረግጡ የመጀመሪያቸው መሆኑን ገልጸው አመጣጣቸው የአገራችንን አጠቃላይ የለውጥ ሂደት ለማየት፣ ለረጅም ጊዜ የናፈቋቸውን ዘመድ ወዳጆች ለማግኘትና የተጀመረውን የሰላም፣ የፍቅርና የመደመር ሂደት በሚችሉት መጠን ለመደገፍ መሆኑን ገልጸዋል።

ምንም አይነት ፖለቲካዊ ውድድር የማድረግም ሆነ ስልጣን የማግኘት ፍላጎት የለኝም ያሉት ኮ/ል ጎሹ በአሁኑ ወቅት በአገራችን የተጀመረው የሰላም፣ የእርቅና የመደመር እንቅሴቃሴ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ በመሆኑ እርሳቸውን ጨምሮ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊደግፈው እንደሚገባ በማመን መምጣታቸውን ጠቁመው ለዚህም ለኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ወጣቱ የሰላምን አስፈላጊነት በሚገባ ተገንዝቦ ለግጭት ከሚዳርጉ እንቅስቃሴዎች እንዲቆጠብ ጥሪ አቅርበው ማንኛውንም ጥያቄዎች በሰላማዊ መንገድ በማቅረብ መፍትሄ ማግኘት የሚያስችል ሁኔታ ተፈጥሯል የሚል እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል።

ለዚህም ያላቸውን ልምድና ተሞክሮ ለማጋራትና ለሰላማዊ ሂደቱ መጎልበት የተቻላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት ቃል ገብተዋል።

ምንጭ፡- የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

No comments:

Post a Comment