የቦ ታክስ

ለዲያስፓራ አባላት አሁን ኢትዮጵያ ላላችሁ። የአሜሪካ ታክሳችሁን ካላችሁበት ሆናችሁ እንድታሰሩ ነገሮችን ሁሉ አስተካክለናል። ያልተሰራ የታክስ ውዝፍ (Back Tax)፣ መስተካከል ያለበት ታክስ (Amendment), የዚህ አመት ታክስ እና ሌሎችንም እንሰራለን።በViber ሆነ Whatspp ይደውሉልን። 619 255 5530 ። YebboTax info@yebbo.com Yebbo.com

Monday, October 29, 2018

ኮ/ል ጎሹ ወልዴ አዲስ አበባ ገቡ

ኮ/ል ጎሹ ወልዴ አዲስ አበባ ገቡ
**********************************
በደርግ ዘመነ መንግስት የአገራችን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና የትምርት ሚኒስትር የነበሩት ኮ/ል ጎሹ ወልዴ ዛሬ አዲሰ አበባ የገቡ ሲሆን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሂሩት ዘመነና እና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአሜሪካ ጉዳዮች ዳ/ጀነራል አቶ ነብያት ጌታቸውን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች አቀባበል አድርግውላቸዋል።

የቀድሞው ሚኒስትር በቦሌ ዓለምአቀፍ አየር መንገድ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የደርግን አገዛዝ በመቃወም ሃላፊነታቸውን በፈቃዳቸው ከለቀቁና ኑሯቸውን በአሜሪካ ካደረጉ ጀምሮ ላለፉት 32 አመታት የአገራቸውን መሬት ሲረግጡ የመጀመሪያቸው መሆኑን ገልጸው አመጣጣቸው የአገራችንን አጠቃላይ የለውጥ ሂደት ለማየት፣ ለረጅም ጊዜ የናፈቋቸውን ዘመድ ወዳጆች ለማግኘትና የተጀመረውን የሰላም፣ የፍቅርና የመደመር ሂደት በሚችሉት መጠን ለመደገፍ መሆኑን ገልጸዋል።

ምንም አይነት ፖለቲካዊ ውድድር የማድረግም ሆነ ስልጣን የማግኘት ፍላጎት የለኝም ያሉት ኮ/ል ጎሹ በአሁኑ ወቅት በአገራችን የተጀመረው የሰላም፣ የእርቅና የመደመር እንቅሴቃሴ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ በመሆኑ እርሳቸውን ጨምሮ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊደግፈው እንደሚገባ በማመን መምጣታቸውን ጠቁመው ለዚህም ለኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ወጣቱ የሰላምን አስፈላጊነት በሚገባ ተገንዝቦ ለግጭት ከሚዳርጉ እንቅስቃሴዎች እንዲቆጠብ ጥሪ አቅርበው ማንኛውንም ጥያቄዎች በሰላማዊ መንገድ በማቅረብ መፍትሄ ማግኘት የሚያስችል ሁኔታ ተፈጥሯል የሚል እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል።

ለዚህም ያላቸውን ልምድና ተሞክሮ ለማጋራትና ለሰላማዊ ሂደቱ መጎልበት የተቻላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት ቃል ገብተዋል።

ምንጭ፡- የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

No comments:

Post a Comment

Note: Only a member of this blog may post a comment.

Curated Products for Generation X

https://amzn.to/3VhbwJz GenX Essentials - Curated Products for Generation X ...

Do you need Ethiopian Power of Attorney where your agent can preform several crucial tasks on your behalf? Such as adoption proceedings, buying movable or immovable properties, paying tax, represent you in governmental and public offices and several others tasks with our your physical presence? If your answer is yes get the Ethiopian Power of Attorney or YEBBO now on sale

Shop Amazon