የቦ ታክስ

ለዲያስፓራ አባላት አሁን ኢትዮጵያ ላላችሁ። የአሜሪካ ታክሳችሁን ካላችሁበት ሆናችሁ እንድታሰሩ ነገሮችን ሁሉ አስተካክለናል። ያልተሰራ የታክስ ውዝፍ (Back Tax)፣ መስተካከል ያለበት ታክስ (Amendment), የዚህ አመት ታክስ እና ሌሎችንም እንሰራለን።በViber ሆነ Whatspp ይደውሉልን። 619 255 5530 ። YebboTax info@yebbo.com Yebbo.com

Friday, November 2, 2018

Tallest building in Addis adds two more stories

በኢትዮጵያ ረጅሙ ህንፃ የ2 ወለል ከፍታ ጭማሪ አደረገ
************************************************* 

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለዋና መስሪያ ቤትነት በአዲስ አበባ እያስገነባው የሚገኘውን ህንፃ ከ46 ወለል ወደ 48 ወለል ከፍ አደረገ፡፡

ባንኩ የዋና መስሪያ ቤቱ ግንባታ የወለል ከፍታ እንዲጨምር ያደረገው ቀድሞ በነበረው ባለ 46 የወለል ከፍታ ድዛይን ላይ ማሻሻያ በማድረግ ነው፡፡

እስከ 2012 ዓ.ም መጨረሻ አካባቢ ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቀው ህንፃው ከ200 ሜትር በላይ በሚሆነው ርዝመቱ ከምስራቅ አፍሪካ የሚወዳደረው የለም ተብሏል፡፡

ህንፃውን ሙሉ ለሙሉ ገንብቶ ለማጠናቀቅ ወደ 300 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ወጪ እንደሚፈጅም ነው ከባንኩ የተገኘው መረጃ የሚያመለክተው፡፡

በቻይና የመንግስት ግንባታ ኮርፖሬሽን (CSCEC) በ150 ሺህ ሜትር ስኩዌር ቦታ ላይ እየተገነባ ያለው ይኸው የምስራቅ አፍሪካ ረጅሙ ህንፃ በተጨማሪም 2 ባለ 5 ወለል የስብሰባ ማእከልና አጠቃላይ አገልግሎት ህንፃዎችን ያካተተ ዘመናዊ ህንፃ ነው፡፡

በዚሁ የህንፃ ግንባታ ከወለል በታች ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ የምድር ውስጥ ወለሎችንም ያቀፈ ነው፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ የንግድ ማእከል በሆነው የብሄራዊ ቲያትር አካባቢ እየተገነባ የሚገኘው ህንፃው፤ በአራቱም ማዕዘናት ከተማዋን ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡

የህንፃው ግንባታ ሲጠናቀቅ በከተማዋ ውስጥ ከሚገኙ በቱሪስት ከሚጎበኙ ቦታዎች አንደኛው እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡

የህንፃው የመጨረሻው የወለል ክፍልም ለጎብኝዎች ክፍት ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ፎቶግራፎቹ በመገንባት ላይ ከሚገኘው ህንፃ አናት ላይ የሚታየውን የአዲስ አበባ ከተማ ገፅታ የሚያሳዩ ናቸው፡፡
በናትናኤል ፀጋዬ

No comments:

Post a Comment

Note: Only a member of this blog may post a comment.

Curated Products for Generation X

https://amzn.to/3VhbwJz GenX Essentials - Curated Products for Generation X ...

Do you need Ethiopian Power of Attorney where your agent can preform several crucial tasks on your behalf? Such as adoption proceedings, buying movable or immovable properties, paying tax, represent you in governmental and public offices and several others tasks with our your physical presence? If your answer is yes get the Ethiopian Power of Attorney or YEBBO now on sale

Shop Amazon