የቦ ታክስ

ለዲያስፓራ አባላት አሁን ኢትዮጵያ ላላችሁ። የአሜሪካ ታክሳችሁን ካላችሁበት ሆናችሁ እንድታሰሩ ነገሮችን ሁሉ አስተካክለናል። ያልተሰራ የታክስ ውዝፍ (Back Tax)፣ መስተካከል ያለበት ታክስ (Amendment), የዚህ አመት ታክስ እና ሌሎችንም እንሰራለን።በViber ሆነ Whatspp ይደውሉልን። 619 255 5530 ። YebboTax info@yebbo.com Yebbo.com

Friday, November 2, 2018

Visa on arrival to All African in Addis Ababs

ኢትዮጵያ ለመላው አፍሪካ ዜጎች የመዳረሻ ቪዛ መስጠት ጀምራለች
*************************

ኢትዮጵያ ከጥቅምት 20 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ ለሁሉም የአፍሪካ አገራት ህዝቦች በቦሌ አለም ዓቀፍ የአውሮፕላን ጣቢያ የመዳረሻ ቪዛ አገልግሎት መስጠት ጀምራለች።

የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ  ሂሩት ዘመነ ጥቅምት 22 ቀን 2011 ዓ.ም የአገልግሎቱን መጀመር በተመለከተ በአፍሪካ ህብረት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ለህብረቱ አባል አገራት አምባሳደሮችና ተወካዮች እንዲሁም ለህብረቱ ኮሚሽንና የተ.መ.ድ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ተወካዮችና ባልደረቦች ገለፃ አድርገዋል።

ሚኒስትር ዴኤታዋ ኢትዮጵያ በህብረቱ 2063 አጀንዳ የበለጠ ትኩረት የተሰጠው የበለጸገች፣ የተዋሃደችና ሰላም የሰፈነባት አፍሪካን የመፍጠር የቆየ ራዕይ እውን እንዲሆን እየሰራች መሆኑን ገልጸው  በኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አመራር ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት የራዕዩ አንድ ዋና አካል የሆነውን ነፃ አህጉራዊ የሰዎች ዝውውር እውን የማድረግ እንዲሁም አዕምሮዎችን ለገንቢ ሃሳብና ገበያዎችን ለጋራ ንግድ ክፍት የማድረግ ቁልፍ የህብረቱ ግቦችን ለማሳካት አገልግሎቱ እንዲጀመር መደረጉን አስረድተዋል።

አገራችን ሌሎች ተመሳሳይ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ የአፍሪካ አገራትን መቀላቀሏ የህብረቱን የነፃ ንግድ ኢንቨስትመንትና ቱሪዝም ፍሰትና ትስስሮችን የሚያሰፋና የአህጉራዊ ውህደት አጀንዳውን ተፈፃሚነት የሚያፋጥን እንደሚሆንም ገልጸዋል። አህጉራዊ የአየር ትራንስፖርትና የመሰረተ ልማት ትስስሮች እንዲፋጠኑ እንደሚያግዝም ጠቅሰዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወጣቱና ሴቶች የአገር ፕሬዝዳንትነት፣ የካቢኔ ሹምነት፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንትነትን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ ከፍተኛ ሃላፊነቶችን በስፋት እንዲይዙ ማድረጋቸውም የህብረቱ ቁልፍ አጀንዳዎች የሆኑትን አህጉራዊ የወጣትና ጾታዊ ተሳትፎ የማሳደግ አጀንዳዎች ከማሳካት አንጻር በሞዴልነት የሚጠቀስ ነው ብለዋል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ አገራችን አገልግሎቱን መጀመሯ የአፍሪካ የፖለቲካ መዲናነቷን እንደሚያሳድገው ገልጸው፣ ሌሎች የህብረቱ አባል አገራትም ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገ/ማርያም በበኩላቸው፣ አየር መንገዱ የአፍሪካ ኩራት እንደመሆኑ ከህብረቱ አባል አገራት ቁጥር በላይ 59 የአፍሪካ መዳረሻዎች ያሉት መሆኑን ጠቁመው የተጀመረው የመዳረሻ ቪዛ አገልግሎት ቀልጣፋ እንዲሆን በ59ኙም የአየር መንገዱ የአፍሪካ መዳረሻዎች በሚገኙ ጽ/ቤቶቹ ከተጓዦች የቪዛ ማመልከቻና ክፍያ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በማስጨረስ አገራዊና አህጉራዊ ግዴታውን እንደሚወጣ አስታውቀዋል።

የኢፌዴሪ ኢሚግሬሽንና የዜግነት ጉዳዮች ዋና መምሪያ በበኩሉ ለአገልግሎቱ መሳለጥ በቂ ዝግጅት ማድረጉን አስታውቋል። በተጨማሪም አፍሪካውያንን ጨምሮ ለተለያዩ ዲፕሎማሲያዊ ግልጋሎቶችም ሆነ ሌሎች ቋሚ ስራዎች፣ ለኢንቨስትመንት፣ ንግድና ወዘተ ለሚመጡ የሌላ አገር ዜጎች ከ5-10 አመታት የሚያገለግል ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ይፋ አድርጓል።

የህብረቱ አባል አገራት ተወካዮች በበኩላቸው አገራችን የወሰደችው እርምጃ የሚደነቅ መሆኑንና ቀሪ አባል አገራትም ተመሳሳይ መንገድ ሊከተሉ ይገባል ብለዋል።

አገራችን ከመላው አለም ወደ አገራችን ለቱሪዝም መምጣት ለሚፈልጉ ሁሉ በኢንተርኔት ማመልከቻ አቅርበው ሲፈቀድላቸው ተገቢውን ክፍያ በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ ሲፈጽሙ የመዳረሻ ቪዛ የሚያገኙበትን አሰራር መጀመሯ የሚታወስ ነው።

ምንጭ:-  የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

No comments:

Post a Comment

Note: Only a member of this blog may post a comment.

Curated Products for Generation X

https://amzn.to/3VhbwJz GenX Essentials - Curated Products for Generation X ...

Do you need Ethiopian Power of Attorney where your agent can preform several crucial tasks on your behalf? Such as adoption proceedings, buying movable or immovable properties, paying tax, represent you in governmental and public offices and several others tasks with our your physical presence? If your answer is yes get the Ethiopian Power of Attorney or YEBBO now on sale

Shop Amazon