Shop Amazon

Monday, November 16, 2020

Ethiopia:Medical personnel were sent to the front lines to provide medical support to the Defense Forces

ለመከላከያ ሠራዊት የሕክምና ድጋፍ ለመስጠት ወደ ጦር ግንባር ለሚያመሩ የሕክምና ባለሙያዎች አሸኛኘት ተደረገ 
**********************

ለኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የሕክምና ድጋፍ ለመስጠት ወደ ጦር ግንባር ለሚያመሩ የሕክምና ባለሙያዎች በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አሸኛኘት ተደርጓል።

በአሸኛኘቱ ላይ የከተማዋ ምክትል ከንቲባ አዳነች አበቤ፣ የከተማዋ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዮሐንስ ጫላን ጨምሮ በርካታ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። 

ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ ሐኪሞቹ ለመከላከያ ኃይላችን ሙያዊ ድጋፍ ለማድረግ በመወሰናቸው አመስግነው፣ ለሕክምና ባለሙያዎችም ሆነ ለመከላከያ ሠራዊቱ አስፈላጊው ድጋፍ ሁሉ እንደሚደረግላቸው ገልጸዋል። 

የጤና ባለሙያዎቹ ወደ 1.7 ሚሊዮን ብር የሚገመት የሕክምና ግብዓት ከአዲስ አበባ አስተዳደር ተረክበዋል። 

የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዮሐንስ ጫላ በዚህ ወቅት "የጤና ባለሙያች የመከላከያ ሠራዊቱን ለማገልገል ዕድል በማግኘታቹ እንኳን ደስ  አላችሁ" ብለዋል።

የሕክምና ድጋፍ ለመስጠት የሚሄዱት ባለሙያዎች 10 ስፔሳሊስት ዶክተሮች፤ 24 ነርሶች፤ አንድ ማደንዘዣ የሚሰጥ ስፔሻሊስት ዶክተርን ጨምሮ 48 የሕክምና ባለሙያዎች በሁለት ቡድን ተከፍለው እንደሚጓዙ ተገልጿል። 

በዋለልኝ ተዓምር 

Medical personnel were sent to the front lines to provide medical support to the Defense Forces
 **********************

 The Addis Ababa City Administration has provided medical assistance to the FDRE Defense Forces.

 The event was attended by the city's deputy mayor, Adanech Abebe, and the city's health bureau chief, Dr. Yohannes Chalan.

 Deputy Mayor Adanech Abebe thanked the doctors for their professional support and said they would provide all necessary support to the medical staff and the army.

 The health workers received about 1.7 million birr in medical supplies from the Addis Ababa administration.

 Addis Ababa Health Bureau Head, Dr. Yohannes Chala, said, "Congratulations on the opportunity for health professionals to serve the Defense Forces."

 10 specialist doctors to provide medical support;  24 Nurses:  It is said that 48 medical professionals, including an anesthesiologist, are divided into two groups.

 By the miracle of my tall Walelig Taamir)


No comments:

Post a Comment