Thursday, November 19, 2020

ከኅዳር 22 በኋላ በአሮጌ ብር ግብይት መፈጸም እንደማይቻል ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ

ከኅዳር 22 በኋላ በአሮጌ ብር ግብይት መፈጸም እንደማይቻል ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ
******************************

ከኅዳር 22 ቀን 2013 ዓ.ም በኋላ በአሮጌ ብር ግብይት መፈጸም እንደማይቻል ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል፡፡

ብሔራዊ ባንክ ለኢቲቪ በላከው መግለጫ ከኅዳር 22 ቀን 2013 ዓ.ም በኋላ በአሮጌ ብር ግብይት መፈጸም እንደማይቻል ገልጾ፣  አሮጌውን ብር በአዲስ ብር የመቀየሪያ የመጨረሻ ቀን ግን ታኅሣሥ 6 ቀን 2013 ዓ.ም መሆኑን አስታውቋል፡፡

የባንኩ መግለጫ እንደሚያስረዳው፣ እስከ አሁን ያልተቀየረ ብር እንዲቀየር እና ሂደቱን ለማፋጠን ከኅዳር 22 ቀን 2013 ዓ.ም እስከ ታኅሣሥ 6 ቀን 2013 ዓ.ም ባሉት 15 ቀናት በአሮጌ ብር ግብይት መፈጸም አይቻልም፤ ግብይት መፈጸም የሚቻለው በአዲሱ ብር ብቻ ነው፤ በእነዚህ የመጨረሻዎቹ 15 ቀናት ማንኛውም ሰው አሮጌውን ብር ወደ ባንክ ሄዶ መቀየር ግን ይችላል፡፡

ታኅሣሥ 6 ቀን 2013 ዓ.ም የመጨረሻ ብር የመቀየሪያ ቀን መሆኑ ታውቆ ህብረተሰቡ በእጁ ያለውን አሮጌ ብር እንዲቀይር ባንኩ አሳስቧል፡፡


No comments:

Post a Comment

Note: Only a member of this blog may post a comment.

የቦ ታክስ

ለዲያስፓራ አባላት በሙሉ እንዲሁም አሁን ኢትዮጵያ ላላችሁ። የአሜሪካ ታክሳችሁን ካላችሁበት ሆናችሁ እንድታሰሩ ነገሮችን ሁሉ አናስተካክላለናል። ያልተሰራ የታክስ ውዝፍ (Back Tax)፣ መስተካከል ያለበት ታክስ (Amendment) እንችላለን። የዚህ አመት ታክስ እና ሌሎችንም እንሰራለን።በViberም ሆነ Whatspp ይደውሉልን። ስልክ ቁጥራችን 619 255 5530 ነው ። YebboTax info@yebbo.com Yebbo.com

Translate

Do you need Ethiopian Power of Attorney where your agent can preform several crucial tasks on your behalf? Such as adoption proceedings, buying movable or immovable properties, paying tax, represent you in governmental and public offices and several others tasks with our your physical presence? If your answer is yes get the Ethiopian Power of Attorney or YEBBO now on sale

Shop Amazon

Call Yebbo

የቦ ኮሚኒኬሽን ኔት ወርክ ፣ ለ25 አመታት በላይ የስራ ልምድ ያካበተው የእናንተው በእናንተው። ከምሰጣቸው አገልግሎቶች ውስጥ የውክልና አገልግሎት መስጠት የኢትዮጵያ ፓስፖርት አገልግሎት መስጠት የቢጫ ካርድ የማውጣት አገልግሎት የታክስ አገልግሎት መስጠት (የትም የኢትዮጵያ ግዛት ይኑሩ) የጉዞ ወኪል የትርጉም ስራ አገልግሎት ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 619-255-5530 ይደውሉ።