የቦ ታክስ

ለዲያስፓራ አባላት አሁን ኢትዮጵያ ላላችሁ። የአሜሪካ ታክሳችሁን ካላችሁበት ሆናችሁ እንድታሰሩ ነገሮችን ሁሉ አስተካክለናል። ያልተሰራ የታክስ ውዝፍ (Back Tax)፣ መስተካከል ያለበት ታክስ (Amendment), የዚህ አመት ታክስ እና ሌሎችንም እንሰራለን።በViber ሆነ Whatspp ይደውሉልን። 619 255 5530 ። YebboTax info@yebbo.com Yebbo.com

Sunday, November 15, 2020

በሱዳን አብዬ የተሰማራው የ23ኛ ሞተራይዝድ ሰላም አስከባሪ ሻለቃ አመራሮችና አባላት በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይ አስመልክቶ ውይይት አካሄዱ

 

በሱዳን አብዬ የተሰማራው የ23ኛ ሞተራይዝድ ሰላም አስከባሪ ሻለቃ አመራሮችና አባላት በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይ አስመልክቶ ውይይት አካሄዱ
***********************************
በሱዳን አብዬ የተሰማራው የ23ኛ ሞተራይዝድ ሰላም አስከባሪ ሻለቃ አመራሮችና አባላት በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይ አስመልክቶ ውይይት አድርገዋል፡፡
በውይይቱ ላይ የተገኙት በሱዳን አብዬ ሰሜን ቀጣና ላይዘን ኦፊሰር ብ/ጀ ዋኘው አለሜ በበኩላቸው፣ በሰሜን ዕዝ የሰራዊት አባላት ላይ የተፈፀመው ጥቃት እጅግ አሳዛኝና ሊወገዝ የሚገባው መሆኑን ገልፀው፣ በሰላም ማስከበር ተልዕኮ የተሰማራው ሃይል ተረጋግቶ ግዳጁ ላይ ትኩረት በማድረግና አንድነቱን በሚያተናክሩ ስራዎች ላይ መረባረብ ይገባል ብለዋል፡፡
የሻለቃው ዋና አዛዥ ኮ/ል ሐሰን አብደላ፣ መንግስት የጀመረውን ህግ የማስከበር ስራና ወንጀለኞችን ህግ ፊት ለማቅረብ እየወሰደ ያለው ህጋዊ እርምጃ ተገቢና የሚደገፍ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በቀጣይ ውስጣዊ አንድነታችንን የሚያጠናክሩ የግንባታ አቅጣጫዎችን በመከተልና ተልዕኳችን ላይ በማተኮር ቀሪ የግዳጅ ጊዜያቶችን ህዝባችንንና ሃገራችንን በሚያኮራ አኳኋን መፈፀም ይገባናል ብለዋል፡፡
የውይይቱ ተሳታፊዎችም ጥቃቱን አውግዘው በጥቃቱ ሳንረበሽና ሳንደናገጥ ይበልጥ አንድነታችንንና ጓዳዊ ዝምድናችንን አጠናክረን የተሰጠንን ስራና ሃላፊነት በሚገባ በመወጣት የሰላም አምባሳደርነታችንን ማረጋገጥ አለብን ማለታቸውን ከመከላከያ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ

No comments:

Post a Comment

Note: Only a member of this blog may post a comment.

Curated Products for Generation X

https://amzn.to/3VhbwJz GenX Essentials - Curated Products for Generation X ...

Do you need Ethiopian Power of Attorney where your agent can preform several crucial tasks on your behalf? Such as adoption proceedings, buying movable or immovable properties, paying tax, represent you in governmental and public offices and several others tasks with our your physical presence? If your answer is yes get the Ethiopian Power of Attorney or YEBBO now on sale

Shop Amazon