Monday, November 30, 2020

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተፈጠሩ ግጭቶችን አስመልክተው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች:-

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተፈጠሩ ግጭቶችን አስመልክተው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች:-
************************

• በእያንዳንዱ ሳምንት የጦርነት ድግስ ነበር፣ መንግስት ስራ እንዳይሰራ በየቦታው ችግር ይፈጠር ነበር፣ 113 የሚሆኑ ግጭቶች ተፈጥረዋል፡፡

• የብሔር፣ የሃይማኖት ግጭት እንዲነሳ ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል፡፡

• አንድ ጎጃሜ ከጎጃም ወደ አምቦ ሲሄድ ወገኔ ነው ብሎ ነው የሚሄደው፣ ይህ ህዝብ በጥርጣሬ እንዲታያይ ነው ለማድረግ የሞከሩት፡፡

• ባለፈው ሁለት ዓመት ተኩል በኦሮሚያ ውስጥ 37 ግጭቶች ነበሩ፡፡

•  ባለፈው ሁለት ዓመት ተኩል በአማራ ክልል 23 ግጭቶች ነበሩ፡፡

• በአማራ ክልል ቅማንት የወሰድን እንደሆነ ጎንደር ከሁሉም ብሔሮች ጋር አብሮ ለመኖር ልምድ ያለው አከባቢ ነው፣ ቅማንትና አማራ ተብሎ መለየት በማይቻል ደረጃ ነው የህዝቡ አኗኗር፡፡

• በቤንሻንጉል ጉሙዝ  15 ግጭቶች ተከስተዋል፡፡

•  አዲስ አበባ ላይ 14 ግጭቶች ተከስተው ነበር፡፡

• የሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያን በተመለከተ ከሃጫሉ በተጨማሪ ሌሎች የኦሮሞና የአማራ አመራሮችን በመግደል ግጭቱን የኦሮሞና የአማራ ለማስመሰል ጥረት ተደርጓል፡፡

• ከዚያ በኋላ ሃጫሉን አጥተናል እና ሌሎች ጉዳቶች እንዳይደርሱ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡

•  በጋምቤላ 7 ግጭቶች ነበሩ፡፡

• በሚዛን ቴፒ፣ ጉራፈርዳ ግጭቶች ተከስቷል፡፡

• ጉጂና ጌዲዮ እንደ አንድ ቤተሰብ የሚኖር ህዝብ ሲሆን፣ እዚያ አካባቢ ሰዎች እንዲፈናቀሉ ተደርጓል፡፡

• አማራ ክልል፣ ቤኒሻንጉል ያዋስነዋል ተጋጭቷል፣ ኦሮሚያ ያዋስነዋል ተጋጭቷል፣ አፋር ያዋስኗል ተጋጭቷል፣ ትግራይ ያዋስነዋል ነገር ግን አልተጋጨም፡፡

• ሌሎች ክልሎችም ከጎረቤት ክልሎች ጋር እንዲጋጩ ተደርጓል፣ ትግራይ ክልል ጎረቤት ክልል ቢሆንም ከትግራይ ግን አለመጋጨታቸው ግጭቱ ታስቦበት የሚሰራ በመሆኑ ነው፡፡

No comments:

Post a Comment