A Yebbo Global Information Hub

EthioVibes Global

World travel, documents, money, auto, food, culture, history, sports, diaspora, business and technology.

Passport Photo Translation Notary Tax Travel ለኢትዮጵያውያን
Advertisement

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተፈጠሩ ግጭቶችን አስመልክተው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች:-

Published
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተፈጠሩ ግጭቶችን አስመልክተው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች:-
************************

• በእያንዳንዱ ሳምንት የጦርነት ድግስ ነበር፣ መንግስት ስራ እንዳይሰራ በየቦታው ችግር ይፈጠር ነበር፣ 113 የሚሆኑ ግጭቶች ተፈጥረዋል፡፡

• የብሔር፣ የሃይማኖት ግጭት እንዲነሳ ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል፡፡

• አንድ ጎጃሜ ከጎጃም ወደ አምቦ ሲሄድ ወገኔ ነው ብሎ ነው የሚሄደው፣ ይህ ህዝብ በጥርጣሬ እንዲታያይ ነው ለማድረግ የሞከሩት፡፡

• ባለፈው ሁለት ዓመት ተኩል በኦሮሚያ ውስጥ 37 ግጭቶች ነበሩ፡፡

•  ባለፈው ሁለት ዓመት ተኩል በአማራ ክልል 23 ግጭቶች ነበሩ፡፡

• በአማራ ክልል ቅማንት የወሰድን እንደሆነ ጎንደር ከሁሉም ብሔሮች ጋር አብሮ ለመኖር ልምድ ያለው አከባቢ ነው፣ ቅማንትና አማራ ተብሎ መለየት በማይቻል ደረጃ ነው የህዝቡ አኗኗር፡፡

• በቤንሻንጉል ጉሙዝ  15 ግጭቶች ተከስተዋል፡፡

•  አዲስ አበባ ላይ 14 ግጭቶች ተከስተው ነበር፡፡

• የሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያን በተመለከተ ከሃጫሉ በተጨማሪ ሌሎች የኦሮሞና የአማራ አመራሮችን በመግደል ግጭቱን የኦሮሞና የአማራ ለማስመሰል ጥረት ተደርጓል፡፡

• ከዚያ በኋላ ሃጫሉን አጥተናል እና ሌሎች ጉዳቶች እንዳይደርሱ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡

•  በጋምቤላ 7 ግጭቶች ነበሩ፡፡

• በሚዛን ቴፒ፣ ጉራፈርዳ ግጭቶች ተከስቷል፡፡

• ጉጂና ጌዲዮ እንደ አንድ ቤተሰብ የሚኖር ህዝብ ሲሆን፣ እዚያ አካባቢ ሰዎች እንዲፈናቀሉ ተደርጓል፡፡

• አማራ ክልል፣ ቤኒሻንጉል ያዋስነዋል ተጋጭቷል፣ ኦሮሚያ ያዋስነዋል ተጋጭቷል፣ አፋር ያዋስኗል ተጋጭቷል፣ ትግራይ ያዋስነዋል ነገር ግን አልተጋጨም፡፡

• ሌሎች ክልሎችም ከጎረቤት ክልሎች ጋር እንዲጋጩ ተደርጓል፣ ትግራይ ክልል ጎረቤት ክልል ቢሆንም ከትግራይ ግን አለመጋጨታቸው ግጭቱ ታስቦበት የሚሰራ በመሆኑ ነው፡፡

Comments