Call Yebbo

YebboTax Ethiopian Banner
ለአሜሪካ ታክስ ከፋዮች፣ አመታዊ ታክሳችሁን፣ ያልተሰራ የታክስ ውዝፍ (Backtax)፣ መስተካከል ያለበት ታክስ (Amdment) ካላችሁ የትም ሆናችሁ ማሰራት ትችላለችሁ።የኢትዮጵያ ፓስፖርት፣ የቢጫ ካርድ፣ ውክልና፣ የትርጉም ስራ ይፈልጋሉ? በViber/WhatsApp በ619 255 5530 ደውሉልን። info@yebbo.com Yebbo.com

Monday, November 16, 2020

በትግራይ ክልል መቀሌ ሀራ ገበያ ዓዲ ጉደም ምድር ባቡር ፕሮጀክት በሚጠብቁት ላይ ከተፈጸመ ጥቃት የተረፉት ሁለት የፌደራል ፖሊስ አባላት አዲስ አበባ ከተማ ገብተዋል፡፡

በትግራይ ክልል መቀሌ ሀራ ገበያ ዓዲ ጉደም ምድር ባቡር ፕሮጀክት በሚጠብቁት ላይ ከተፈጸመ ጥቃት የተረፉት ሁለት የፌደራል ፖሊስ አባላት አዲስ አበባ ከተማ ገብተዋል፡፡
***********************************************
አዲስ አበባ፣ህዳር፣07-2013 ዓ.ም

የህዝብና መንግስት መሰረተ ልማቶችን በመጠበቅ ከ10 ዓመታት በላይ መቆየታቸውን የገለጸው ዋና ሳጅን ድረስ ስንሻው የተለመደዉን መደበኛ የጥበቃ ስራችን እያከናወን በነበርንበት ወቅት በፕሮጀክቱ ባሉ ሳይቶች ላይ የነበሩ የስራ ባልደረቦቻችንን ትጥቅ በማስፈታት፣ አፍነውና እጃቸውን በካቴና አስረው ወደ መቀለ ሲወስዷቸው እጃችንን ከምንሰጥ ብለን ወደ ጫካ በመግባት ለሚተኮስብን ተኩስ ምላሽ በመስጠት ለማምለጥ ችለናል ብለዋል፡፡

እኛ ለአንድ ብሔር የቆምን ሳይሆን ከሁሉም ብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የተውጣጣንና ሀገራችን ኢትዮጵያ በአንድነት ስንጠብቅ የኖርን በመሆኑ እንደዚህ አይነት የሀገር ክህደት ይፈጸምብናል ብለን አልጠበቅንም ነበር በማለት ገልጸዋል፡፡

የታፈኑ አባሎቻችንን ለማስለቀቅ ብንሞክርም ከአቅማችን በላይ በመሆናቸውና እኛንም ለማስቀረት ከፍተኛ የሆነ ቶክስ ስለ ከፈቱብን ለጽንፈኛው ቡደኑ እጅ ከምንሰጥ በማለት ለሶስት ቀናት የሚበላና የሚጠጣ ባልነበረበት በበረሃ ጫካ ለጫካ እየተጓዘን አፋር ክልል ስንደርስ አባላ የሚባል አካባቢ የክልሉ ህዝብ ተቀብሎን ወደ መስመር አወጣን ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የህወሓት ጽንፈኛ ቡድኑ በእኛ በፌደራል ፖሊስ አባላትና በሀገር መከላከያ ሰራዊት የፈጸመው አረመናዊ ድርጊት በጣም አሳዝኖናል፣በተለይ ከ10 ዓመታት በላይ አብሮን የሰሩና የኖሩ የትግራይ ተወላጅ የፖሊስ አባላት ወደ ክልሉ ልዩ ሀይል በመቀላቀል አፈሙዝ ወደ እኛ በማዞር የፈጸሙብን ክህደት በጣም አሳዝኖናል፣ አስከፍቶናልም ብለዋል፡፡
 
ከዚህ ቀደም አባት አርበኞች ከፍተኛ መስዋትነት ከፍለው ኢትዮጵያን እንዳስረከቡን ሁሉ ዛሬም በርካታ የሀገር ተቆርቃሪ የሆኑ ጓዶች ስላሉን ሀገራችን ለማዳን እየተከናወኑ ያሉ የህግ ማስከበር ስራዎች ስኬታማ እንዲሆኑ እስከ መጨረሻ ከህዝብ ጋር በመቆም ለዚህ አስነዋሪ ድርጊት የተሰለፉትን የህወሓት ፅንፈኛ ቡድን ለህግ ለማቅረብ ለሚደረገው ርብርብ ኃላፍነታቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡

 ሌላኛዉ የሰሜን ዲቪዥን፣ሶስት፣ሻለቃ 4፣ሻምበል 1 አባል ኮንስታብል ድረስ ንጉሴ እኛ ሰላም ነው ብለን በተቀመጥንበትና ባላሰብነው ሰዓት የክልሉ ልዩ ሃይልና ሚሊሻ ተደራጅተው በመምጣት አንድ ዳቦ ለሁለት በመካፈል አብረውን ሲበሉ ከነበሩ ከትግራይ ተወላጅ የስራ ባልደረቦቻችን ጋር በመሆን ጥቃት ቢፈጽሙብንም የአፋር ህዝብ ላደረገልን አቀባበልና ድጋፍ ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል፡፡

እኛ የትግራይ ህዝብን ከወንጀል በመከላከልና በክልሉ የሚገኙ መሰረተ ልማቶችን በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ማህበራዊ እንቅስቃሴ ስናግዝና ስንተባበር ነው የቆየነው፣የትግራይ ህዝብ ይህንን ጽንፈኛ ቡድን በማጋለጥ ነጻነቱን ሊያረጋግጥ ይገባልም ብሏል፡፡

No comments:

Post a Comment

Note: Only a member of this blog may post a comment.

Do you need Ethiopian Power of Attorney where your agent can preform several crucial tasks on your behalf? Such as adoption proceedings, buying movable or immovable properties, paying tax, represent you in governmental and public offices and several others tasks with our your physical presence? If your answer is yes get the Ethiopian Power of Attorney or YEBBO now on sale

Shop Amazon