"በትግራይ ክልል በሚገኙ ባንኮች ሒሳብ የከፈቱ እና ከትግራይ ውጭ ያሉ ደንበኞች በያሉበት አካባቢ ሒሳባቸውን ማንቀሳቀስ እንዲችሉ ተፈቅዷል"፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ
******************
በፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ በወንጀል ተጠርጥረው ሂሳባቸው እንዳይንቀሳቀስ ከተደረገው ደንበኞች በስተቀር በትግራይ ክልል በሚገኙ ባንኮች ሒሳብ የከፈቱ እና ከትግራይ ውጭ ያሉ ደንበኞች በያሉበት አካባቢ ሒሳባቸውን ከዛሬ ኅዳር 23 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ማንቀሳቀስ እንዲችሉ መፈቀዱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለኢቢሲ በላከው መግለጫ አስታወቀ።
በትግራይ ክልል እየተከናወነ ባለው የሕግ ማስከበር እንቅስቃሴ ጋር በተገናኘ የፀጥታው ሁኔታ ለባንኮች አመቺ በሆነባቸው ከተሞች ባንኮች ተከፍተው ሥራ እንዲጀምሩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከሚመለከታቸው ጋር እየሠራ መሆኑን ባንኩ አስታውቋል።
የፀጥታው ሁኔታ አመቺ ባልሆነባቸው ከተሞች ደግሞ ባንኮች ተዘግተው የሚቆዩ መሆኑን ነው የገለጸው።
በትግራይ እየተካሄደ ባለው የሕግ ማስከበር እንቅስቃሴ ምክንያት የፀጥታው እና የኔትወርክ ሁኔታ እስኪሻሻል ባንኮች ተዘግተው እንዲቆዩ መወሰኑ ይታወሳል።
"Banks opened in banks in Tigray Region and allowed outside of Tigray to move their accounts wherever they are": National Bank of Ethiopia
******************
The National Bank of Ethiopia (NBE) said in a statement to ABC that customers who have opened accounts in banks in the Tigray Region and outside Tigray have been allowed to move their accounts from November 23, 2013.
The National Bank of Ethiopia (NBE) said it is working with stakeholders to reopen banks in Tigray State.
He said banks would remain closed in insecure cities.
It is to be recalled that due to the ongoing law enforcement activities in Tigray, it was decided to keep the banks closed until the security and network situation improves.
No comments:
Post a Comment