Shop Amazon

Wednesday, January 5, 2022

Ministry of Education to build 50 modern boarding schools" - Prof. Berhanu Nega

“ትምህርት ሚኒስቴር 50 ዘመናዊ አዳሪ ትምህርትህን ቤቶችን ያስገነባል” - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
*******************

ትምህርት ሚኒስቴር በመላ ኢትዮጵያ 50 ዘመናዊ ደረጃቸውን የጠበቁ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ለማስገንባት የሚያስችል ፕሮጀክት ማዘጋጀቱን የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስታወቁ።

በትምህርት ቤቶቹ የዲዛይን ዝግጅቱ ላይም ከኢትዮጵያ አርክቴክቶች ማኀበር ጋር ውይይት እያካሄደ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢንተርኔት አማራጭ የቪዲዮ መልዕክታቸው፤ በኢትዮጵያ 48 ሺህ ትምህርት ቤቶች ቢኖሩም ደረጃቸውን የጠበቁት 0 ነጥብ 01 በመቶዎቹ ብቻ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በአጠቃላይም ስድስት ትምህርት ቤቶች ብቻ ናቸው ደረጃ አራት ላይ የሚገኙት ብለዋል።

ስለዚህም ኢትዮጵያ ደረጃቸውን የጠበቁ የአካልና የአዕምሮ ማበልጸጊያ ትምህርት ቤቶች ያስፈልጓታል፤ ለዚህም ደረጃቸውን የጠበቁ አዳዲስ ትምህርት ቤቶችን መገንባት አለብን ብለዋል።

የኢትዮጵያ አርክቴክቶች ማኀበር በበጎ ፈቃደኝነት የትምህርት ቤቶቹን የግንባታ ዲዛይን ለማዘጋጀት ፈቃደኛ መሆኑን የገለጹት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፤ በዚህ አገራዊ ፕሮጀክት ለመሳተፍ ፈቃደኝነታቸውን ላሳዩ ኢንጂነሮችም ምስጋና አቅርበዋል።

የፕሮጀክቱን አጠቃላይ ዝግጅት በተመለከተ የኢትዮጵያ አርክቴክቶች ማኀበር አመራርና አባላት ከትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ኢፕድ ዘግቧል።
"Ministry of Education to build 50 modern boarding schools" - Prof. Berhanu Nega
 *******************

 The Ministry of Education has prepared a project to build 50 state-of-the-art boarding schools across Ethiopia, according to the Minister of Education, Prof. Berhanu Nega.

 He said discussions are underway with the Ethiopian Architects Association on the design of the schools.

 Minister of Education, Prof. Berhanu Nega's online video message;  He said there are 48,000 schools in Ethiopia but only 01.01 percent have met their standard.

 In total, he said, only six schools are in Level Four.

 Therefore, Ethiopia needs standard physical and mental enrichment schools;  "We need to build new schools that are up to standard," he said.

 According to Prof. Berhanu, the Ethiopian Architects Association is willing to design the construction of the schools.  He also thanked the engineers who volunteered to participate in this national project.

 According to the report, the leadership and members of the Ethiopian Architects Association have held discussions with the leadership of the Ministry of Education regarding the overall preparation of the project.
 

No comments:

Post a Comment