Shop Amazon

Friday, April 5, 2024

የእስራኤል ጦር ኃይል ለሁለት ሳምንታት ያህል በጋዛው አል-ሺፋ ሆስፒታል ላይ ወረራ ካካሄደ በኋላ አብዛኛውን የህክምና ተቋሙን ክፍል ለቆ መውጣቱ ተገለጸ።

 የእስራኤል ጦር ኃይል ለሁለት ሳምንታት ያህል በጋዛው አል-ሺፋ ሆስፒታል ላይ ወረራ ካካሄደ በኋላ አብዛኛውን የህክምና ተቋሙን ክፍል ለቆ መውጣቱ ተገለጸ።

በሆስፒታሉ ላይ ከተካሄደው ወረራ እና ጥቃት በኋላ የጋዛው ሆስፒታል ሕንፃ አፅሙ ቀርቶ ታይቷል።
የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት እንደገለጸው ወታደሮቹ በመቶዎች የሚቆጠሩ “ሽብርተኞችን” ገድለዋል እንዲሁም በቁጥጥር ሥር አውለዋል።
ሠራዊቱ “በሆስፒታሉ ዙሪያ” የጦር መሣሪያዎች እና የደኅንነት መረጃዎች ማግኘቱን ገልጧል።
በሐማስ የሚመራው የጋዛ ጤና ሚኒስቴር በርካታ ሬሳዎችን ጥሎ ለመሄድ መገገዱን አሳውቋል። የአካባቢው ሰዎች ደግሞ ሥፍራው መውደሙን ይናገራሉ።
የእስራኤል ጦር፤ በአል-ሺፋ ሆስፒታል ላይ ወረራ እና ጥቃት የፈጸመው ሐማስ መልሶ ስለተደራጀበት መሆኑን ይገልጣል።
በእስራኤል አየር ድብደባው ምክንያት በሆስፒታሉ ዙሪያ ያሉ ሕንፃዎችንም ጭምር ያጠቃ ነበር። የእስራኤል ጦር የሆስፒታሉን የሕክምና ክፍሎች ያወደምኩት ሐማስ እና የፍልስጤም ኢስላሚክ ጂሀድ ስለሚጠቀሙበት ነው የሚል መግለጫ አውጥቷል።

No comments:

Post a Comment