Friday, November 6, 2020

ከወንበዴው ህዋሃት የጥፋት ተልዕኮ ተቀብለው በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች በህዝብ እልቂት በማድረስ አገርን ለማፍረስ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የጥፋት ቡድኖች በቁጥጥር ሥር

ከወንበዴው ህዋሃት የጥፋት ተልዕኮ ተቀብለው በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች በህዝብ እልቂት በማድረስ አገርን ለማፍረስ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የጥፋት ቡድኖች በቁጥጥር ሥር ዋሉ
*************************

ከወንበዴው ህዋሃት የጥፋት ተልዕኮ ተቀብለው በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች በህዝብ እልቂት በማድረስ አገርን ለማፍረስ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የጥፋት ቡድኖች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስታወቀ፡፡

የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጉዳዩን አስመልክቶ ለኢቲቪ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው ከወንበዴው ህዋሃት የጥፋት ተልዕኮ ተቀብለው በጋምቤላ ክልል በብሔር ብሄረሰቦች መካከል ግጭት በመፍጠር አካበቢውን የትርምስ ቀጠና ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሀይሎች በተደረገባቻው ጥብቅ ክትትል በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውሷል፡፡

የዚህ የጥፋት ቡድን አካል የነበሩ ነገር ግን ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ተልዕኮቸውን በድብቅ ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ አለም ደስታ ሃየሎምና ጋትክቦም የተባሉ የጥፋት ቡድኑ ተጠርጣሪዎች ባሉበት ታድነው በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል፡፡

ቀደም ሲል ይፋ በተደረገው መረጃ ላይ እንደተመለከተው፤ በህዝብ ላይ እልቂት በመፈጸም ክልሉን የትርምስ ቀጠና ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ ከነበሩት ተጠርጣሪዎች መካከል ጸጋዬ መብርሃቱ (ካህሳይ)፣ ገብረማሪያም አናንያ፣ ዋስትና ተሾመ (ጃል ሴና)፣ አብርሃም መሃሪ፣ ኮሎኔል ተስፋዬ (ባሌስትራ) እና በድምሩ 19 የወንበዴው የህዋሃትና የኦነግ ሸኔ የጥፋት ኃይሎች በቁጥጥር እንደዋሉ መግለጫው አስታውሷል።

በተመሳሳይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመተከል ዞን ተፈጽሞ የነበረውን ተመሳሳይ ጥፋት በአሶሳና ካማሼ ዞኖች ብሔር ብሄረሰቦችን በማጋጨት አካበቢውን የትርምስ ቀጠና በማድረግ በህዝብ ላይ እልቂት ለመፈጸም ከወንበዴው ህዋሃት የጥፋት ቡድን አባል ከሆነው አባይ ፀሃዬ ተልዕኮ ወስደው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ተጥራጥሪዎች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መገለፁ ይታወቃል፡፡

 የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መግለጫ እንዳመለከተው፤ በተጨማሪም አራት የወንበዴው የህዋሃት የጥፋት ቡድን አባላት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ ተደርጓል። 

የተያዙት አራት የዚህ የጥፋት ቡድን አባላት ተጠርጣሪዎችም ተክላይ ገብረ መድህን ፣ ፍሰሃ ወልደ እግዚአብሄር ፣ አብርሃ ገብረ ሚካኤል እና ተስፋ ገብረ ሚካኤል የተባሉ መሆናቸውን አገልግሎቱ በላከው መግለጫ አስታውቋል። 

ከወንበዴው ህዋሃት የጥፋት ቡድን ተልዕኮ በመቀበል በህዝብ ላይ ጭፍጨፋ እንዲፈጸም ስምሪት የተሰጣቸው አራት ከላይ የተገለፁት የጥፋት ሃይሎች በእጃቸው 59 የሚሆኑ የባንክ ደብተሮችን የያዙ ሲሆን፤ ተክላይ ገብረ መድህን የተባለው ተጠርጣሪ በአገር ውስጥ ከሚገኙ የተለያዩ ባንኮች 19 የሂሳብ ደብተሮችን ከፍቶ ሲያንቀሳቅስ ከመቆየቱም በላይ በአንዱ የሂሳብ ደብተር ውስጥ ብቻ ከ12 ሚሊዮን ብር በላይ መገኘቱን መግለጫው ጠቁሟል ። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የማነ ግርማይና ዮሃንስ ግርማይ የተባሉ የህዋሃት የጥፋት ቡድን ተላላኪዎችን ጨምሮ በድምሩ 23 ተጠርጥሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስተውቋል፡፡

ከወንበዴው ህዋሃት የጥፋት ቡድን ተመሳሳይ ተልዕኮ ተቀብለው በአዲስ አበባ ከተማና በዙሪያው በከፍተኛ ባለስልጣናትና በንፁሃን ዜጎች ላይ እንዲሁም በትላልቅ መሰረተ ልማቶች ላይ ለአብነትም ለገዳዲና ገፈርሳ የሚገኙ የውሃ ግድቦች እንዲሁም በለገጣፎ የሚያልፍ ከፍተኛ የውሃ ማስተላለፊያ መስመር ላይ የፈንጂ ጥቃት ለመፈጸም ዝግጅት ሲያደርጉ የቆዩ የኦነግ ሸኔ አባላት ለጥፋት ተልዕኳቸው ካዘጋጇቸው ተቀጣጣይ ፈንጂዎችና ሌሎች ቁሶች ጋር በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ብሄራዊ መረጀና ደህንነት አገልግሎት በላከው መግለጫ ገልፆል፡፡ 

የጥፋት ተልዕኮቸው ባይከሽፍ ኖሮ፤ በህዝቡ ላይ ከፍተኛ ማህበራዊ፤ ኢኮኖሚያዊና ሰብኣዊ ቀውስ ያስከትል እንደነበር መግላጫው አስታውሷል፡፡የዚሁ ጥፋት አካል የነበሩትና የጥፋት ቡድኑ ያሰማራቸው ቶሎሳ አብዲሳ፣ ደጀኔ ፍቃዱ፣ ሀብታሙ ተስፋየ መርጋ፤ ንጉሴ አሰፋና ፈልማት ታከለ የተባሉ ተጠርጣሪዎች መሆናቸውን መግላጫው አመልክቷል፡፡

በሌላም በኩል ጋዲሳ ሞሲሳ ባይሳ የተባለው የጥፋት ቡድኑ አካልና ግብርአበሮቹ በአዲስ አበባ በንጹሃን ዜጎች ላይ የቦንብ ጥቃት ለመፈጸም ካዘጋጇቸው ቦንቦች ጋር በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስተውቋል፡፡

በተለይ የወንበዴው የህዋሃት ቡድን ለጥፋት ተልዕኮው ሽፋን ንስር ጥበቃ ድርጅትን በመጠቀም በስራቸው ከወንበዴው ስልጠና የወስዱ ሃይሎችን በስሩ በማደራጀት በንፁሃን ዜጎች ላይ ጥቃት ለመፋፀምና ጥፋት ለማድረስ በዝግጅት ላይ እያሉ በቁጥጥር ስር እንዲውሉም ተደርጓል፡፡ 

የህዋሃት የጥፋት ቡድን በትግራይ ክልል ሃግቦ በተባለ አካባቢ ወታዳራዊ ስልጠና በመስጠት የገዳይ እስኮድ ቡድን ባለቤትነቱ ሀይሉ በርሄ በቅፅል ስሙ ሀይሉ ሳንቲም ተብሎ በሚጠራው የወንበዴው የጥፋት ቡድን አስተባባሪ ስም በተቋቋመው ንስር የግል ጥበቃ ኤጀንሲ ሽፋን ካስገባ በኃላ ነበር ጥቃት ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ ብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ከፌደራል ፖሊስና ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በቅንጅት ባደረጉት ጥብቅ ክትትል የቡዱኑ አባላትን በቁጥጥር ስር ማዋል የተቻለው፡፡

በተመሳሳይ አዲስ አበባ ሆኖ ለወንበዴው ለህዋሃት የጥፋት ቡድን የተለያዩ መረጃዎችን እያሰባሰበ ሲልክ የነበረና ከኦሮሚያ ወጣቶችን እየመለመለ ለስልጠና ወደ ትግራይ በመላክና የተለያዩ የአመፅ ተልዕኮዎችን ከጥፋት ቡድኑ በመቀበል ኦሮሚያ ክልል ለሚገኙ የኦነግ ሸኔ የጥፋት ቡድኖች ሲያስተላልፍ የነበረው ቶማስ ገብረማሪያም የተባለው ተጠርጣሪም በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጓል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የጥፋት ቡድኑ በኦሮሚያ ክልል በአዳማ፤በሲዳማ ክልል ሃዋሳ፤በደቡብ ክልል ደግሞ በወላይታ፤ ጋሞጎፋ፤ሃድያ፤ስልጤና ጌዲዮ ዞኖች እንዲሁም በሱማሌ ክልል ጅጅጋና በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ተመሳሳይ ትርምስና እልቂት በተላላኪዎች ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ በድምሩ 21 ተጠርጣሪዎች በተለያዩ የጦር መሳሪዎችና መሰል ቁሳቁሶች ጋር በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉን አግልግሎት መስሪያ ቤቱ አስታውቋል፡፡ 

በመጨረሻም ለዚህ ኦፕሬሽን ስኬት የአገራችን ህዝቦች ተሳትፎ የማይተካ ሚና ያለው ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፤ የአገር መከላከያ ሰራዊት፤የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን፤ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፤የክልል ፖሊስ ኮሚሽኖችና ሌሎች የጸጥታ አካላት በቅንጅት ይሄ ዉጤት እንዲመጣ ግዴታቸውን ተወጥተዋል ተብሏል፡፡

ስግብግቡ ጁንታ በህወሓት ውስጥ የመሸገው ኃይል ላይ የተወሰደው የመጀመሪያው ዙር ኦፕሬሽን በስኬት እንደተጠናቀቀ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ

ስግብግቡ ጁንታ በህወሓት ውስጥ የመሸገው ኃይል ላይ የተወሰደው የመጀመሪያው ዙር ኦፕሬሽን በስኬት እንደተጠናቀቀ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ
*************

ባለፉት ሁለት ቀናት ስግብግቡ ጁንታ በህወሓት ውስጥ የመሸገው ኃይል፣ ለስልጣን የሚስገበገበው፣ ለገንዘብ የሚስገበገበው፣ ለሀገር ሉዐላዊነት ለሕዝቦች ደህንነት ደንታ የሌለው ኃይል በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የመከላከያ ሰራዊት እንዲሁም በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የፖሊስ ሰራዊት ላይ ጥቃት መሰንዘሩ ይታወሳል።

ይህ ጥቃት ድንገተኛ ቢሆንም የመጀመሪያው የመከላከል እቅድ ሙሉ ለሙሉ በስኬት መጠናቀቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታውቀዋል።

የእቅዱ ዋነኛ አላማዎች 1ኛ ጥቃቱን መግታት- የመጀመሪያው ዓላማ ጠላት በሁሉም አቅጣጫ ጥቃት እየሰነዘረ በህዝብ፣ በሰራዊቱ፣ በፖሊስ ላይ እና በአንዳንድ ወሳኝ የመሰረተ ልማቶች ላይ የሚያደርሰውን ጥቃት መግታት ነበር። 

ከዚህ አንፃር በተለያየ አካባቢ ይገኝ የነበረ የሀገር መከላከያ ሰራዊትን ወደ ስፍራው በማንቀሳቀስ የጠላትን ጉዞን ሙሉ ለሙሉ በማስቆም ተጨማሪ ጥቃት መሰንዘር ወደማይችልበት ደረጃ ማድረስ ተችሏል ብለዋል።

ሁለተኛው አላማ የመከላከያ እና የፖሊስ ሰራዊት የደረሰበትን ጥቃት ተከትሎ ይህንን ኃይል የመታደግ እና ወሳኝ ሀገራዊ ሀብቶች አና ትጥቆች የመታደግ ስራ እንደነበር ተገልጿል።

ከዚህ አንፃርም በባድመ ግንባር፣ በፆረና እና በዛላንበሳ በዋና ዋና ስፍራ ተሰልፈው ያሉ የሰራዊት አባላት እና ትጥቆች ሙሉ ለሙሉ ከጠላት ፍላጎት ውጭ ለማድረግ ተችሏል።

 
3ኛው አላማ የጠላትን የማድረግ አቅም ማዳከም ነው። የጠላት ኃይል የኢትዮጵያ ህዝብ ከሌለው ሀብት ላይ ቀንሶ ሀገሩን ለመከላከል የገዛቸውን ዋና ዋና ትጥቆች፣ ሚሳኤሎች፣ ሮኬቶች በመጠቀም ጥፋት ማካሄድ እንዳይችል አቅሙን ማዳከም ነበር።

በዚህም ሦስቱ ዓላማዎች መቶ በመቶ መሳካታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።

በተጨማሪም በዳንሻ ግንባር ያለውን ጠላት ሙሉ ለሙሉ በመደምሰስ አካባቢውን መቆጣጠር መቻሉንም አስታውቀዋል።

በቀጣይም ስግብግቡ ጁንታ ሙሉ ለሙሉ ለሕግ እስከሚቀርብ ድረስ የሚደረገው እራስን እና ሀገርን የመከላከል ዘመቻ እንደሚቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አረጋግጠዋል። 

የአየር ሀይሉ በወሰደው እርምጃም በተለያዩ ስፍራዎች ላይ የነበሩ ሮኬቶችን ጨምሮ ሌሎች የተለያዩ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን ሙሉ በሙሉ ለማውደም መቻሉንም ገልፀዋል።

እነዚህ ሮኬቶች እስከ 300 ኪሎ ሜትሮች መወንጨፍ የሚችሉ በመሆናቸው እና በወንጀለኛው ቡድን ሮኬቶቹን የመጠቀም ፍላጎት በመኖሩ በመቀሌ እና አካባቢዋ በነበረው የከባድ መሳሪያ ማስቀመጫ ላይ የአየር ኃይሉ እርምጃ እንዲወስድ መደረጉ ተገልጿል።

በአስማማው አየነው 

Ethiopia, Austria sign air service agreement

ኢትዮጵያ እና ኦስትሪያ የአየር በረራ አገልግሎት ስምምነት ተፈራረሙ 
********************* 

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግሥት ከኦስትሪያ ፌዴራል መንግሥት ጋር እ.ኤ.አ. ታኅሣሥ 10/2013 በአጭር ፊርማ የነበረውን የአየር በረራ አገልግሎት ስምምነት የተሻለ የበረራ ምልልስ እና የሕግ መሠረት በሚሰጥ መልኩ በትላንትናው ዕለት አዲስ አበባ ላይ በተካሄደ የምክክር ስብሰባ አሻሽሎ ተፈራረመ። 

ስምምነቱን በኢትዮጵያ በኩል የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኮ/ል ወሰንየለህ ሁነኛው እና የኦስትሪያ ፌዴራል መንግሥት በኩል ደግሞ በኢትዮጵያ የኦስትሪያ አምባሳደር ሚስተር ሮላንድ ሐውሰር ተፈራርመዋል። 

የስምምነቱ በሙሉ ፊርማ ደረጃ መጠናቀቅ ለብሔራዊ አየር መንገዱ የበረራ መብቶች ሕጋዊ መሠረት የሚሰጥ መሆኑን እና የበረራ ምልልሱንም በየጊዜው በሚኖረው የአየር ትራፊክ ገበያ ልክ ማሳደግ የሚያስችል መሆኑን በባለሥልጣኑ የኢኮኖሚክ ሬጉሌሽንና ስትራተጂክ አመራር ዳይሬክተር አቶ እንደሻው ይገዙ ገልጸዋል። 

እንደ አቶ እንደሻው ገለፃ ስምምነቱ ተወካይ አየር መንገዶች ከበረራ የሚያገኙትን ገቢ ከተደራራቢ ግብር ነፃ የሚያደርግ፣ ከአዲስ አበባ እና ቪዬና ከተሞች በተጨማሪ በከተሞቹ መካከል እና ባሻገር ባሉ ሌሎች መዳረሻ ከተሞች የበረራ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል እና አየር መንገዶችን በሽርክና እንዲሠሩ የሚፈቅድ ነው። 

ስምምነቱ ኢትዮጵያ ከኦስትሪያጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት በበለጠ የሚያጠናክር እና በሀገራዊው የ10 ዓመት መሪ የልማት ዕቅድ ዓለም አቀፍ የበረራ መዳረሻዎችን ቁጥር ማሳደግ በሚል የተጣለውን ግብ ስኬታማነት የሚያረጋግጥ ይሆናል። 

ከዚህ በተጨማሪም የአየር ትራንስፖርቱ ንግድ እና ኢንቨስትመንትን በማበረታታት፣ የወጪ ንግዱን በመደገፍ፣ ቱሪዝምን በማስፋፋት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራና በውጭ ምንዛሪ ግኝት ያለውን ሚና እንደሚያጎለብት ይታመናል ሲል የሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን አስታውቋል። 
Sourcev EBS

በጅማ ከተማ ባለፉት ሁለት ቀናት በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

በጅማ ከተማ ባለፉት ሁለት ቀናት በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
**************** 

በጅማ ከተማ ባለፉት ሁለት ቀናት በተደረገው ድንገተኛ ፍተሻ በህዝብ ላይ ጥቃት ለማድረስ የተዘጋጁ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

በቁጥጥር ስር የዋሉት 8 ሽጉጦች፣ 7 ክላሾች፣ ከ130 በላይ የተለያዩ ጥይቶች፣ የጦር ሜዳ መነፅር እና የተለያዩ አገራት ፓስፖርቶች ከያዙ 31 ተጠርጣሪዎች ናቸው። 

በህዝቦች መካከል ልዩነት በመፍጠር ኢትዮጵያን ወደ ብጥብጥ የሚመሩ አካላትን በፅኑ እንደሚያወግዙም የጅማ ከተማ ነዋሪዎች ገልፀዋል። 

በወቅታዊ የጅማ ከተማና አካባቢው ሰላም ላይ ውይይት እያደረጉ የሚገኙት ነዋሪዎቹ የአካባቢውን ሰላም ነቅቶ ለመጠበቅ መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል። 

በከሀዲው የህውኃት ቡድን በሰሜን ዕዝ የመከላከያ ሠራዊታችን ላይ የተሰነዘረው ጥቃት አሳዛኝ፣ አሳፋሪም ነው ያሉት ነዋሪዎቹ ቡድኑ ድባቅ እስኪመታ ድረስ ከአገር መከላከያ ሠራዊት ጋር በፅናት እንደሚቆሙም ነዋሪዎቹ አረጋግጠዋል። 
በዮናስ ካሳ

Ethiopian Civil Aviation Authority announces closure of Mekelle, Shere, Axum and Humera airports

Ethiopian Civil Aviation Authority announces closure of Mekelle, Shere, Axum and Humera airports


የመቐለ፣ ሽረ፣ አክሱም አና ሁመራ ኤርፖርቶች ለማንኛውም የበረራ አገልግሎት ዝግ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን አስታወቀ
*************************

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ከዛሬ ጥቅምት 27/2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 2 ሰዓት ጀምሮ የመቐለ፣ ሽረ፣ አክሱም አና ሁመራ ኤርፖርቶች ለማንኛውም የበረራ አገልግሎት ዝግ መሆናቸውን አስታወቀ። 

ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ በተመሳሳይ ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት (ኤርሜንስ) በተገቢው የመገናኛ ዘዴ በ(ኖታም) አንዲያውቁት መደረጉንም አስታውቋል።

Thursday, November 5, 2020

Ethiopia, Israel agree to work together on information and security

ኢትዮጵያ እና እስራኤል በመረጃ እና ደህንነት ዘርፍ ተባብረው ለመሥራት ተስማሙ
******************
Ethiopia, Israel agree to work together on information and security ****************** Ethiopia and Israel have agreed to work together in the information and security sector, according to the National Intelligence and Security Service. Israeli Deputy Minister of Security Gadi Yvirkan met with Director General of the National Intelligence and Security Service Demlash Gebremichael. During the meeting, the two countries agreed to work together to fight terrorism, exchange information, transfer technology and build capacity in the Horn of Africa.

"Ethiopia and Israel can work together in the information and security sector to strengthen peace and stability in the Horn of Africa," he said.
For his part, Deputy Foreign Minister Gadi Yvirkan said Ethiopia wants to further strengthen its cooperation with Ethiopia in the information and security sector as it has a significant role to play in maintaining peace and stability in the Horn of Africa.
He also said that Israel supports the change initiated by Ethiopia in the information sector. 



ኢትዮጵያ እና እስራኤል በመረጃ እና ደህንነት ዘርፍ ተባብረው ለመሥራት ስምምነት ላይ መድረሳቸውን የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት አስታወቀ።
የእስራኤል ደህንነት ምክትል ሚኒስትር ጋዲ ይቫርካን ከብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄነራል ኮሚሽነር ደምላሽ ገብረሚካኤል ጋር ተገናኝተው ውይይት አድርገዋል።
በውይይታቸውም ሁለቱ አገራት በአፍሪካ ቀንድ ሽብርተኝነትን በጋራ ለመዋጋት፣ የመረጃ ልውውጥ ለማድረግ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሁም በአቅም ግንባታ ዘርፍ ይበልጥ ተባብረው ለመሥራት መስማማታቸውን አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያ እና እስራኤል በመረጃ እና ደህንነት ዘርፉ ተባብረው ቢሠሩ በአፍሪካ ቀንድ እና አካባቢው ሰላም እና መረጋጋት በማጠናከር በኩል ትልቅ አስተዋጽኦ ሊያበረክቱ ይችላሉ ሲሉ ኮሚሽነር ደምላሽ በውይይቱ ገልጸዋል።
ምክትል ሚኒስትር ጋዲ ይቫርካን በበኩላቸው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ሰላም እና መረጋጋት በማስፈን ረገድ ትልቅ ሚና ያላት እና ተሰሚ በመሆኗ ምክንያት እስራኤል ከኢትዮጵያ ጋር በመረጃ እና ደህንነት ዘርፉ ያላትን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር ትፈልጋለች ብለዋል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ በመረጃ ዘርፍ የጀመረችውን ለውጥ እስራኤል እንደምትደግፍም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ እና እስራኤል በመረጃ እና ደህንነት ዘርፍ በጋራ ለመሥራት የደረሱትን ስምምነት በቅርቡ ወደ ተግባር ይሸጋገራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት የላከው መረጃ አመልክቷል።

Sudan says it is tightly controlling its border with Ethiopia via Kesela


 Sudan says it is tightly controlling its border with Ethiopia via Kesela 
Fesah al-Rahman al-Amin, the governor of Kesela state, said security forces have been beefed up in Sela State, one of Sudan's borders with Ethiopia.
This decision was made in light of the Ethiopian government's response to the TPLF.
He also said that the security forces in the area have been instructed to keep the border vigilant and prevent any individuals or groups from entering Sudan with weapons.


He also said that the force at Wade al-Helio, near the border, had been instructed to study the situation.
However, in order to receive the innocent citizens who come to Sudan seeking asylum; With this in mind, a special committee has been appointed to assist in the execution of orders, he said.
Source: Al-Sudani




ሱዳን በከሰላ በኩል ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰንበት ድንበሯ ጥብቅ ቁጥጥር እያደረገች መሆኗን ገለፀች

***************************************************
የከሰላ ግዛት አስተዳዳሪ ፈታህ አል ራሀማን አል አሚን እንዳስታወቁት ከዛሬ ጀምሮ ሱዳንን ከኢትዮጵያ ከምትዋሰንባቸው ድንበሮች አንዱ በሆነው ከሰላ ግዛት አካባቢ ያለው የድንበር ጥበቃ በፀጥታ ኃይሉ እንዲጠናከር ተደርጓል።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው የኢትዮጵያ መንግስት በሕወሐት ላይ እየወሰደ ያለውን እርምጃ ከግምት በማስገባት ነው።
በአካባቢው ያለው የፀጥታ ኃይል ድንበሩን በንቃት እንዲጠብቅና ማንኛውም ግለሰብም ሆነ ቡድን የጦር መሳርያ ይዞ ወደ ሱዳን እንዳይገባ እንዲያደርግ መታዘዙንም አስተዳዳሪው ፈታህ አልራሃማን ተናግረዋል።
በድንበሩ አቅራቢያ ባለችው ዋድ አል ሄሊኦ ያለው ኃይል ሁኔታዎችን በደንብ እንዲያጠና መታዘዙንም ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ ጥገኝነት ፈልገው ወደ ሱዳን የሚመጡትን ንፁሃን ዜጎች ለመቀበል እንዲቻል፤ ይህን ከግምት ባስገባ መልኩ ትዕዛዞች እንዲፈፀሙ ይረዳ ዘንድ ጉዳዩን የሚከታተል ልዩ ኮሚቴም መሰየሙን አስተዳዳሪው አስታወቀዋል።
ምንጭ:- አልሱዳኒ

The airspace in the northern Ethiopian Tigray region is closed for any flight.


 The airspace in the northern Ethiopian Tigray region is closed for any flight and we recommend that no aircraft pass this warning.
Ethiopian Civil Aviation Authority *************************** It is to be recalled that the Ethiopian Civil Aviation Authority has announced to all international countries that international and domestic flights crossing the northern Ethiopian airspace have been closed for any flight service since October 25, 2013. In addition, the airline in the northern Ethiopian region of Tigray is closed for any flight, and we urge you to refrain from flying any aircraft.

በሰሜን የኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ውስጥ ያለው የአየር ክልል ለማንኛውም በረራ የተዘጋ በመሆኑ ይህንን ማሳሰቢያ ተላልፎ በረራ የሚፈጽም ማንኛውም አውሮፕላን እንዳይኖር እናሳስባለን

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን
*************************
ከጥቅም 25/2013 ዓ.ም ጀምሮ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን በሰሜን የኢትዮጵያ የአየር ክልል ውስጥ የሚያቋርጡ የአለም አቀፍ እና የሃገር ውስጥ የበረራ መስመሮች ለማንኛውም የበረራ አገልግሎት የተዘጉ መሆኑን ለሁሉም አለም አቀፍ አገሮች ማስታወቁ የሚታወስ ነው፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ በሰሜን የኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ውስጥ ያለው የአየር ክልል ለማንኛውም በረራ የተዘጋ በመሆኑ ይህንን ማሳሰቢያ ተላልፎ በረራ የሚፈጽም ማንኛውም አውሮፕላን እንዳይኖር እናሳስባለን::

Tuesday, November 3, 2020

ጦርነቱ ተጀመረ!

ሕወሐት በትግራይ በሚገኘው የመከላከያ ካምፕ ላይ ጥቃት አድርሷል። ሰሜን ዕዝንም ለመዝረፍ ሙከራ አድርጓል። ይህ ሠራዊት ከሃያ ዓመታት በላይ የትግራይን ሕዝብ ሲጠብቅ የቆየ ሠራዊት ነው። በቦታው የሚገኘውም የትግራይን ሕዝብ ከጥቃት ለመከላከል ነው። ሕወሐት ግን እንደ ባዕድና እንደ ወራሪ ሀገር ሠራዊት ቆጥሮ። የመከላከያ ሠራዊቱን ለመምታትና ለመዝረፍ ተነሥቷል። በዳልሻሕ በኩልም ጦርነት ከፍቷል።

መንግሥት የትግራይ ሕዝብ እንዳይጎዳ በማሰብ፣ ጦርነት እንዳይፈጠር የትእግሥቱ ጫፍ ድረስ ታግሷል። ጦርነት የሚቀረው ግን በአንድ ወገን ፍላጎት ብቻ አይደለም። 
 
የመከላከያ ሠራዊታችን በኮማንድ ፖስት እየተመራ ሀገሩን የማዳን ተልዕኮውን እንዲወጣ ትእዛዝ ተሰጥቶታል።  ቀዩ መሥመር የመጨረሻው ነጥብ ታልፏል። ሀገርና ሕዝብ ለማዳን ሲባል ኃይል የመጨረሻው አማራጭ ሆኗል። 

የኢትዮጵያ ሕዝብ ነገሮችን በሰከነ መንፈስ እንዲከታተል፣ በየአካባቢው ሊከሠቱ የሚችሉ ትንኮሳዎች  በንቃት እንዲቃኝና ከመከላከያ ሠራዊታችን ጎን እንዲቆም ጥሪ አቀርባለሁ።

የኢፌዴሪ ጠ/ሚ/ር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

Sunday, October 25, 2020

Trump wants to bomb Africa

ADDIS ABABA, Ethiopia (AP) — Ethiopia on Saturday denounced “belligerent threats” over the huge dam it has nearly completed on the Blue Nile River, a day after U.S. President Donald Trump said downstream Egypt will “blow up” the project it has called an existential threat.

Without naming Trump or the U.S., the statement by Prime Minister Abiy Ahmed’s office came amid an outcry in Ethiopia over Trump’s latest threat over the dam. The $4.6 billion Grand Ethiopian Renaissance Dam is a source of national pride, aimed at pulling millions of people from poverty.

“The man doesn’t have a clue on what he is talking about,” Former Prime Minister Hailemariam Dessalegn tweeted, calling Trump’s remark reckless and irresponsible.

Trump made the comment while announcing that Sudan would start to normalize ties with Israel. Downstream Sudan is a party to the talks with Ethiopia and Egypt over the disputed dam. “They (Egypt) will end up blowing up the dam,” Trump said. “And I said it and I say it loud and clear … they’ll blow up that dam. And they have to do something.”

The U.S. president earlier this year told the State Department to suspend millions of dollars in aid to Ethiopia because of the dam dispute, angering Ethiopians who had accused the U.S. of being biased during its earlier efforts to broker a deal on the project among Ethiopia, Egypt and Sudan. Ethiopia walked away from those talks.

“They will never see that money unless they adhere to that agreement,” Trump said Friday.

“Occasional statements of belligerent threats to have Ethiopia succumb to unfair terms still abound,” Ethiopia’s statement said Saturday. “These threats and affronts to Ethiopian sovereignty are misguided, unproductive, and clear violations of international law.”

It added: “Ethiopia will not cave in to aggressions of any kind.”

There was no comment from the Egyptian government on Trump’s remarks, but pro-government media covered them extensively.

Egypt has repeatedly said it wants to settle the dispute through diplomatic means, but it has said it would use “all available means” to defend the interests of its people.

Ethiopia celebrated the first filling of the dam in August, citing heavy rains, to the dismay of Egypt. Ethiopia later banned flights over the dam amid concerns over possible military action by Egypt.

Now, with Trump’s new remarks, some Ethiopians are urging Ethiopian Americans to help vote him out of office in next month’s election.

The statement by Abiy’s office said the talks with Egypt and Sudan have shown significant progress since the African Union has stepped in to oversee them. Trump’s statement could undermine that process, said Abel Abate Demissie, an associate fellow at Chatham House, adding that it proves the U.S. wasn’t an honest broker from the start.

Ethiopia says the colossal dam could help it become a major power exporter. Egypt depends on the Nile to supply its farmers and a booming population of 100 million with fresh water.

Negotiators have said key questions remain about how much water Ethiopia will release downstream if a multi-year drought occurs and how the countries will resolve any future disputes. Ethiopia rejects binding arbitration at the final stage.

A military strike on the dam would be disastrous, one water expert warned. The dam already has more than 4.9 billion cubic meters of water in its reservoir,” Abebe Yirga told The Associated Press. “It will affect thousands of people along the way if this huge amount of water gushes out of the dam.”

The Blue Nile joins the White Nile in Sudan to become the Nile, and about 85% of the river's flow originates from Ethiopia. Officials hope the dam, now more than three-quarters complete, will reach full power-generating capacity in 2023.

 

Related: The second and final presidential debate

Slideshow preview image
 
20 PHOTOS
The second - and final - presidential debate
SEE GALLERY

Saturday, October 24, 2020

Ethiopia blasts Trump remark that Egypt will 'blow up' dam

ADDIS ABABA, Ethiopia (AP) — Ethiopia on Saturday denounced “belligerent threats” over the huge dam it has nearly completed on the Blue Nile River, a day after U.S. President Donald Trump said downstream Egypt will “blow up” the project it has called an existential threat.

Without naming Trump or the U.S., the statement by Prime Minister Abiy Ahmed’s office came amid an outcry in Ethiopia over Trump’s latest threat over the dam. The $4.6 billion Grand Ethiopian Renaissance Dam is a source of national pride, aimed at pulling millions of people from poverty.

“The man doesn’t have a clue on what he is talking about,” Former Prime Minister Hailemariam Dessalegn tweeted, calling Trump’s remark reckless and irresponsible.

Trump made the comment while announcing that Sudan would start to normalize ties with Israel. Downstream Sudan is a party to the talks with Ethiopia and Egypt over the disputed dam. “They (Egypt) will end up blowing up the dam,” Trump said. “And I said it and I say it loud and clear … they’ll blow up that dam. And they have to do something.”

The U.S. president earlier this year told the State Department to suspend millions of dollars in aid to Ethiopia because of the dam dispute, angering Ethiopians who had accused the U.S. of being biased during its earlier efforts to broker a deal on the project among Ethiopia, Egypt and Sudan. Ethiopia walked away from those talks.

“They will never see that money unless they adhere to that agreement,” Trump said Friday.

“Occasional statements of belligerent threats to have Ethiopia succumb to unfair terms still abound,” Ethiopia’s statement said Saturday. “These threats and affronts to Ethiopian sovereignty are misguided, unproductive, and clear violations of international law.”

It added: “Ethiopia will not cave in to aggressions of any kind.”

There was no comment from the Egyptian government on Trump’s remarks, but pro-government media covered them extensively.

Egypt has repeatedly said it wants to settle the dispute through diplomatic means, but it has said it would use “all available means” to defend the interests of its people.

Ethiopia celebrated the first filling of the dam in August, citing heavy rains, to the dismay of Egypt. Ethiopia later banned flights over the dam amid concerns over possible military action by Egypt.

Now, with Trump’s new remarks, some Ethiopians are urging Ethiopian Americans to help vote him out of office in next month’s election.

The statement by Abiy’s office said the talks with Egypt and Sudan have shown significant progress since the African Union has stepped in to oversee them. Trump’s statement could undermine that process, said Abel Abate Demissie, an associate fellow at Chatham House, adding that it proves the U.S. wasn’t an honest broker from the start.

Ethiopia says the colossal dam could help it become a major power exporter. Egypt depends on the Nile to supply its farmers and a booming population of 100 million with fresh water.

Negotiators have said key questions remain about how much water Ethiopia will release downstream if a multi-year drought occurs and how the countries will resolve any future disputes. Ethiopia rejects binding arbitration at the final stage.

A military strike on the dam would be disastrous, one water expert warned. The dam already has more than 4.9 billion cubic meters of water in its reservoir,” Abebe Yirga told The Associated Press. “It will affect thousands of people along the way if this huge amount of water gushes out of the dam.”

The Blue Nile joins the White Nile in Sudan to become the Nile, and about 85% of the river's flow originates from Ethiopia. Officials hope the dam, now more than three-quarters complete, will reach full power-generating capacity in 2023.

 

Related: The second and final presidential debate

Slideshow preview image
 
20 PHOTOS
The second - and final - presidential debate
SEE GALLERY

Thursday, October 22, 2020

እውነተኛውን የብር ኖት ከሀሰተኛውን እንዴት መለየት ይችላሉ?

እውነተኛውን የብር ኖት ከሀሰተኛውን እንዴት መለየት ይችላሉ?

• የገንዘቡ ቁጥሮች በሚያጎላ ማሽን ሲታዩ ከጥቁር ወደ አረንጓዴ ፍሎረሰንት ቀለም ይለወጣሉ፡፡
• የብሩን ዋጋ የሚገልጽ፤ ማየት የተሳናቸው በእጅ ዳሰሳ ማወቅ የሚችሉበት የደህንነት መጠበቂያ አለው፡፡
• የብር ኖቱ ሲዳሰስ የመጎርበጥ ስሜት አለው፡፡
• ገንዘቡ ወደላይ ወይም ወደታች ሲዞር የሚንቀሳቀስ ደማቅ የቀለም ፍንጣቂ ይታያል፡፡
• የሚሽከረከር ደማቅ ቀለም ኮከብ አዲስ የደህንነት መጠበቂያ ክር፤ በክሩ ውስጥ NBE፣ ኢብባ እና የገንዘብ አይነት ተጽፎ ይገኛል፡፡
• ገንዘቡ ወደ ብርሃን አቅጣጫ ተደርጎ ሲታይ በላዩ ላይ ከሚገኘው ምስል ፊት ለፊት ተመሳሳይ ደብዛዛ የውሃ መልክ ያለው ምልክት ይታያል፡፡
• የብር ኖቶች ከብርሃን አቅጣጫ ሲታዩ ኳስ መሳይ ምልክት ከገንዘቡ በስተኋላ ካለው ተመሳሳይ ምልክት ጋር በፍጹም ትይዩ ሆነው በአንድ ላይ ያርፋሉ፡፡
• አንበሳው ምስል ራስ ላይ አልትራቫዮሌት ጨረር ሲበራበት ወደ ቢጫነት የሚለወጥ ፊሎረሰንት ምልክት እንዳለው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/EBCworld
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ

ከ2 ሚሊዮን በላይ አዲሱ የብር ኖት በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የገንዘብ ዝውውር መመሪያን በመተላለፍ በግለሰብ ቤት ውስጥ
የተከማቸ ከ2 ሚሊዮን በላይ አዲሱ የብር ኖት በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።
******************
ወቅታቂ የገንዘብ ዝውውርን አስመልክቶ የባንክ አዋጅ 591/2008 እንደሚያስረዳው በአንድ ግለሰብ እጅ መገኘት ያለበት የብር መጠን 1.5 ሚሊዮን እና ከዚያ በታች ሲሆን ይህንን ተላልፎ ከተጠቀሰው የብር መጠን በላይ ይዞ የተገኘ ግለሰብ ገንዘቡ እንደሚወረስ በግልጽ ተቀምጧል ፡፡ 
 ጥቅምት 7 ቀን 2013 ዓ.ም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ቦታው ዶምቦስኮ ት/ቤት አካባቢ በግለሰብ ቤት ውስጥ የተከማቸ ገንዘብ ስለመኖሩ  ህብረተሰቡ ለፖሊስ ባደረሰው መረጃ መሠረት በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል።
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የልዩ ልዩ ወንጀሎች ምርመራ ቲም ሀላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ይርጋ ተካ እንደገለፁት በህዝብ ጥቆማ የተያዘው 2 ሚሊዮን 222 ሺህ አዲሱ የብር ኖት በቁጥጥር ስር የዋለው  የብሄራዊ ባንክ መመሪያን በመተላለፍ በግለሰብ እጅ መገኘት ከሚፈቀደው በላይ ሆኖ በመገኘቱ ነው።
ህብረተሰቡ የገንዘብ ዝውውር መመሪያውን በመተግበር ተባባሪ እንዲሆን እና መመሪያውን በመተላለፍ የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችን እንዲጠቁም ምክትል ኢንስፔክተር ይርጋ ተካ  ይርጋ ተካ አሳስበዋል።
ዘገባ ፡- ኮንስታብል ኤቢሳ ጅሩ