Shop Amazon

Saturday, October 22, 2016

Ethiopia Announces Restrictions Under State of Emergency (English and Amharic Version)

ክፍል አንድ


የተከለከሉ ተግባራት


ንዑስ ክፍል አንድ
በማንኛውም የሀገሪቱ ክፍሎች የተከለከሉ ተግባራት
አንቀፅ 1. ሁከትና ብጥብጥ የሚያስነሳ ቅስቀሳና ግንኙነት ማድረግ
ማንኛውም ሁከት፣ ብጥብጥና በህዝቦች መካከል መጠራጠርና መቃቃር የሚፈጥር፣ ይፋዊም ሆነ ድብቅ ቅስቀሳ በማናቸውም መልኩና ዘዴ ማድረግ፣ፅሁፍ ማዘጋጀት፣ ማተምና ማሰራጨት፣ ትእይንት ማሳየት፣ በምልክት መግለፅ ወይም መልእክትን በማናቸውም ሌላ መንገድ ለህዝብ ይፋ ማድረግ፣ፍቃድ ሳይኖር ማንኛውንም ህትመት ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት ወይም ወደ ውጪ ሀገር መላክ፤ መልእክት በኢንተርኔት፣ በሞባይል፣ በፅሁፍ፣በቴሌቭዥን፣ በፌድዮ፣ በማህበራዊ ሚድያ ወይም ሌሎች የግንኙነት ዘዴዎች መለዋወጥ።

አንቀፅ 2. ከሽብርተኛ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት ማድረግ
በሽብር ከተሰየሙ ድርጅቶች እና ከፀረ ሰላም ቡድኖች ጋር ማናቸውንም ግንኙነት ማድረግ፣ የአሽባሪ ድርጅቶችን የተለያዩ ፅሁፎች መያዝማሰራጨት፣ አርማቸውን መያዝ ወይም ማስተዋወቅ፣ የቴሌቪዥን ወይም የሬድዮ ፕሮግራምን መከታተል፣ የኢሳት፣ የኦ.ኤም.ኤን. እና የመሳሰሉትንየሽብርተኛ ድርጅቶች ሚዲያዎችን ማሳየት፣ መከታተልና ሪፖርት ማድረግ የተከለከለ ነው።

አንቀፅ 3. ያልተፈቀደ ሰልፍና የአደባባይ ስብሰባ
የህዝብና የዜጎች ሰላምና ፀጥታ ለማስጠበቅ ሲባል ከኮማንድ ፓስቱ ፈቃድ ውጭ ማናቸውም ሰልፍና የአደባባይ ስብሰባ ማድረግ የተከለከለ ነው።

አንቀፅ 4. ለህዝብ አገልግሎት አለመስጠት
(1)
ህዝብ የሚጠቀምባቸውን ወይም ፈቃድ የወጣባቸው የንግድ ስራዎች፣ ሱቆች ወይም የመንግስት ተቋማት መዝጋት ወይም ምርትና አገልግሎትማቋረጥ፣ ከስራ ቦታ ያለ በቂ ምክንያት መጥፋት ወይም ስራ ማቆም፣ ተገቢውን አገልግሎት አለመስጠት፣ ስራን መበደል፣
(2)
የመንግስት ወይም የግል ተቋማት ሰራተኞች ወደ መደበኛ ስራቸው እንዳይገቡ መዛትና ማስፈራራት የተከለከለ ነው።

አንቀፅ 5. በትምህርት ተቋማት አድማ ማድረግ
በትምህርት ቤቶች፣ በዩኒቨርስቲዎች እና በሌሎች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመማር ማስተማር ሂደትን የሚያውክ አድማ ማድረግ፣ የትምህርትተቋማትን መዝጋት ወይም በነዚህ ተቋማት ላይ ጉዳት ማድረግ የተከለከለ ነው።

አንቀፅ 6. በስፖርት ማዘውተሪያዎች አድማ ማድረግ
በስፖርት ማዘውተሪያ ማእከላት ከስፖርታዊ ጨዋነት ውጪ የሆኑ ሁከቶችን፣ ብጥብጦችን መፍጠር የተከለከለ ነው።

አንቀፅ 7. የተሽከርካሪዎችን እንቅስቃሴ ማወክ
የተሽከርካሪ፣ የእግረኛ እና ሌሎች የመጓጓዣ ዘዴዎችን እንቅስቃሴ መንገድ በመዝጋት በዛቻ እና በሌሎች መሰል ድርጊቶች ሰላማዊ እንቅሰቃሴንማወክ፣ አገልግሎት ማስተጓጎል፣ የመጓጓዣ ዋጋ ታሪፍ መጨመር፣ የሚመለከተው አካል ከደለደለው የስራ ስምሪት ውጪ መሆን የተከለከለ ነው።

አንቀፅ 8.በመሰረተ ልማቶችና ሃይማኖታዊ ተቋማት ላይ ጉዳት ማድረስ
በግል በህዝብና በመንግስት ማናቸውም ተቋማት፣ በመሰረተ ልማት፣ በኢንቨስትመንትና በሌሎች የልማት አውታሮች እንዲሁም በሃይማኖታዊተቋማት ላይ በማንኛውም መንገድ ጉዳት ማድረስ ወይም ዘረፋ መፈፀም የተከለከለ ነው።

አንቀፅ 9. ህዝባዊና ብሄራዊ በዓላትን ማወክ
ህዝባዊና ብሄራዊ በዓላትን በማንኛውም ሁኔታ ማወክ፣ ማደናቀፍ ወይም ከበዓሉ አላማ ጋር የማይገናኙ የፖለቲካ አጀንዳዎች ወይም መፈክሮችንበማንኛውም መንገድ ማስተጋባት የተከለከለ ነው።

አንቀፅ 10. ሀይማኖታዊ፣ ባህላዊና ህዝባዊ በዓላት ላይ ቅስቀሳ ማድረግ
ሀይማኖታዊ ተቋማት ውስጥ በሚደረጉ ስብከቶችና ትምህርቶች ሀይማኖታዊ አስተምህሮት ከማድረግ ውጪ በህዝቦች መካከል መጠራጠርናመቃቃርን የሚፈጥር፣ በህብረተሰቡ ላይ ስጋት የሚፈጥር፣ ሁከትና ብጥብጥ የሚቀሰቅስ ቅስቀሳ ማድረግ የተከለከለ ነው።

አንቀፅ 11. የህግ አስከባሪዎችን ስራ ማወክ
የህግ አስከባሪ አካላት የሚሰጡትን ማንኛውም ትዕዛዝ አለማክበር ስራቸውን ማደናቀፍ፣ ለፍተሻ አለመተባበር ወይም እንዲቆም ሲጠየቅ አለማቆም፣ኬላዎችን ጥሶ ማለፍ የተከለከለ ነው፡፡ በህግ አስከባሪ አካላት ባልደረቦች ላይ ጥቃት መፈፀም ወይም ለመፈፀም መሞከር የተከለከለ ነው፣

አንቀፅ 12. ያተፈቀደ አልባሳት መልበስ
የህግ አስከባሪ ሃይሎችን ዩኒፎርም መልበስ፣ ይዞ መገኘት፣ በቤት ማስቀመጥ፣ አሳልፎ መስጠትና መሸጥ ክልክል ነው።

አንቀፅ 13. የጦር መሳሪያ ይዞ መግባት
ማናቸውም የጦር መሳሪያ፣ ስለት ወይም እሳት የሚያስነሱ ነገሮችን ወደ ገበያ፣ ሀይማኖት ተቋማት፣ ህዝባዊ በአላት የሚከበሩበት ወይም ወደማናቸውም ህዝብ የሚሰበሰብበት ቦታ ይዞ መግባት የተከለከለ ነው።

አንቀፅ 14. ትጥቅን በሶስተኛ ሰው እጅ እንዲገባ ማድረግ
ማንኛውም የህግ አስከባሪ አካላት ባልደረባ ወይም ማንኛውም ህጋዊ ትጥቅ ያለው ሰው ትጥቁን በማንኛውም ሁኔታ በሶስተኛ ሰው እጅ እንዲገባማድረግ ክልክል ነው።

አንቀፅ 15. መቻቻልን እና አንድነትን የሚጎዳ ተግባር መፈፀም
ማንነትን ወይም ዘርን መሰረት ያደረገ ማንኛውም አይነት ጥቃት መፈፀም ወይም ጥቃት እንዲፈፀም የሚያነሳሳ ንግግር መናገር የተከለከለ ነው።



አንቀፅ 16. የሀገርን ሉዓላዊነት፣ ደህንነት፣ ህገመንግስታዊ ስርዓት የሚጎዳ ተግባር መፈፀም
ማንኛውም ሰው ከውጭ መንግስታትም ሆነ ከውጭ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር የሀገር ሉአላዊነት፣ ደህንነትና ህገ-መንግስታዊ ስርዓትንሊጎዳ የሚችል ግንኙነትና የመልዕክት ልውውጥ ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡ ማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ የሀገርን ሉዓአላዊነት፣ ደህንነት እና ህገ መንግስታዊ ሥርዓቱን {የሚፃረር} ማናቸውም ጋዜጣዊ መግለጫ ለሀገር ውስጥም ሆነ ለውጭ ሚዲያዎች መስጠት ክልክል ነው።

አንቀፅ 17. ያልተፈቀደ ቦታ መገኘት
ከስደተኛ ካምፕ አግባብ ካለው አካል ከሚሰጥ ፈቃድ ውጭ መውጣት ወይም ህጋዊ ቪዛ ሳይኖረው ወደ ሀገር ውስጥ መግባት የተከለከለ ነው።

አንቀፅ 18. ያለፈቃድ ስለሚደረግ የዲፕሎማቶች እንቅስቃሴ
የኮማንድ ፖስቱ እውቅናና ፈቃድ ሳያገኙ ዲፕሎማቶች ለራሳቸው ደህንነት ጥበቃ ሲባል ከአዲስ አበባ ከአርባ /40/ ኪሎ ሜትር ራዲየስ ውጪመንቀሳቀስ የተከለከለ ነው።

አንቀፅ 19. የህግ አስከባሪ አካላት ግዳጅ ላይ ስለመገኘት
ማንኛውም የህግ አስከባሪ አካል ባልደረባ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተፈፃሚ በሚሆንበት ጊዜ ከስራ መልቀቅ ወይም አስገዳጅ ሁኔታ ካልተፈጠረበስተቀር የአመት እረፍት ፍቃድ መውሰድ ክልክል ነው።

አንቀፅ 20. የህዝብን ሰላምና ፀጥታ ለማደፍረስ ድጋፍ ማድረግ
በዚህ መመሪያ የተከለከሉ ተግባራትን በመተላለፍ ህገ ወጥ ድርጊት የሚፈፅሙ ሰዎችን፣ በገንዘብና በቁሳቁስ ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድመደገፍ እንዲሁም ከለላ መስጠት፣ መደለያ መስጠት፣ ማበረታታት የተከለከለ ነው።

ንዑስ ክፍል ሁለት

በተወሰኑ
የሀገሪቱ አካባቢዎች እንዳይፈፀሙ የተከለከሉ ተግባራት
ከላይ በንዑስ ክፍል አንድ የተደነገነገው እንደተጠበቀ ሆኖ ከአንቀፅ 21-24 የተዘረዘሩት ክልከላዎች ኮማንድ ፖስቱ እየወሰነ ይፋ በሚያደረጋቸውቦታዎች ወይም አካባቢዎች ላይ ተፈፃሚ ይሆናሉ።

አንቀፅ 21. የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ
ማናቸውም የጦር መሳሪያ፣ ስለት ወይም እሳት የሚያስነሱ ነገሮችን ከግቢውና ይዞታው ውጪ ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው።

አንቀፅ 22. በልማት አውታሮችና መሰረተ ልማቶች ላይ የሚሰነዘር ጥቃት
የኢኮኖሚ አውታሮች፣ መሰረት ልማትና የኢንቨስትመንት ተቋማት፣ የእርሻ ልማቶች፣ በፋብሪካዎች እና በመሰል ተቋማት አካባቢ ከቀኑ 12 ሰዓትበኋላ እስከ ንጋት 12 ሰአት ድረስ ከተፈቀደለት ሰራተኛ በስተቀር ማንኛውም ሌላ ሰው መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው፡፡ ከላይ በተመለከቱት ቦታዎች የሰዓት እላፊውን ተላልፎ በተገኘ ማንኛውም ሰው ላይ የጥበቃ ወይንም የህግ አስከባሪ አካላት አስፈላጊውን እርምጃእንዲወስዱ ስልጣን ተሰጥቷቸዋል።

ክፍል ሁለት

የተከለከሉ ተግባራት ተፈጽሞ ሲገኝ ስለሚወሰዱ የአስቸኳይ ጊዜ እርምጃዎች

አንቀጽ.23. ስለ ሰዓት እላፊ
ማናቸውም ሰው በኮማንድ ፖስቱ ውሳኔ የሰዓት እላፊ በይፋ በሚገለጽበት ቦታና ጊዜ የሰዓት እላፊ ክልከላን በመተላለፍ ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስአይፈቀድም፡፡

አንቀጽ 24. ሁከትን ለማስቆምና አደጋን ለመከላከል የሚደረግን እንቅስቃሴ ማወክ
ሰላምና ፀጥታን ሊያደፈርሱ ይችላሉ ተብለው የሚጠረጠሩ ሰዎች ወይም ቡድኖችን ወይም ለጉዳት ተጋላጭ ናቸው ተብለው የሚገመቱ ሰዎችወይም ቡድኖች ወደ ተወሰነ አካባቢ ወይም ህንፃ እንዳይገቡ ወይም በተፈቀደላቸው አንድ የተወሰነ አካባቢ ብቻ እንዲቆዩ የተሰጠውን ትዕዛዝመተላለፍ ክልክል ነው፡፡ ለአካባቢው ደህንነት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት ወደ ተዘጋ መንገድ ማንም ሰው እንዳይገባ ኮማንድ ፖስቱ የሰጠውንእግድ ወይም ክልከላ መተላለፍ ክልክል ነው፡፡

ንዑስ ክፍል ሶስት
መረጃ የመስጠትና የማስታወቅ ግዴታ

አንቀጽ 25. የተከራይ መረጃ የመያዝና የመስጠት ግዴታ
ማንኛውም ቤት፡ ቦታ፡ ክፍል ወይም ተሽከርካሪ ወይም ተመሳሳይ መገልገያ አከራይ የሆነ ሰው የተከራዩን ማንነት በዝርዝርና በጹሁፍ የመያዝናበአቅራቢያው ላለ ፖሊስ ጣቢያ በሃያ አራት ሰዓት ውስጥ የማሳወቅ ግዴታ አለበት፡፡ በተጨማሪም የውጭ አገር ዜጋን ያከራየ እንደሆነ የፓስፖርቱንኮፒና የኪራዩን ውል በአቅራቢያው ላለ ፖሊስ ጣቢያ የማሳወቅ ግዴታ አለበት፡፡

አንቀጽ 26. መረጃ የመስጠት ግዴታ
የህዝብ ሰላምና ፀጥታ ለማስጠበቅ ሲባል ማንኛውም ተቋም መረጃ እንዲሰጥ በየደረጃው ባለ የህግ አስከባሪ አካል ሲጠየቅ የመስጠትና የመተባበርግዴታ አለበት። አንቀጽ 27. እርምጃ ለመውሰድ ስልጣን ስላለው ሰው
ከላይ በክፍል አንድ ከአንቀጽ 1- 24 የተመለከቱ የተከለከሉ ተግባራትን ፈጽመው በተገኙ ሰዎችና ድርጅቶች ላይ የህግ አስከባሪዎች እናባልደረቦቻቸው በአዋጁና በዚህ መመሪያ የተዘረዘሩ የሚከተሉትን የአስቸኳይ ጊዜ እርምጃዎችን ሊወስዱ ይችላሉ፡፡

አንቀጽ 28. ክልከላዎች ሲጣሱ ስለሚወሰዱ እርምጃዎች
ከላይ በክፍል አንድ የተመለከቱ ክልከላዎችን ተላልፎ በተገኘ ማንኛውም ሰው ላይ የህግ አስከባሪዎች
(1)
ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ በቁጥጥር ስር ማዋል፣
(2)
አዋጁ ተፈጻሚነቱ እስከሚያበቃበት ጊዜ ድረስ ኮማንድ ፖስቱ በሚወስነው ቦታ እንዲቆይ ማድረግ፣
(3)
ተገቢውን የተሃድሶ ትምህርት በመስጠት የሚለቀቀውን እንዲለቀቅ፣ ወደ ፍርድ ቤት
የሚቀርበውን ደግሞ እንዲቀርብ ማድረግ፣
(4)
ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ በማናቸውም ሰዓት ብርበራ ማድረግ፣ የአካባቢውን ህዝብና ፖሊስ በማሳተፍ ማንኛውንም ወንጀል የተፈጸመበት ወይምሊፈጸምበት የሚችል ንብረት መያዝ ወይም ንብረቱ ባለበት እንዲጠበቅ ማድረግ፣
(5)
በማንኛውም ሬድዮ ቴሌቪዥን ጽሁፍ ምስል ፎቶ ግራፍ ቲያትርና ፊልም
የሚተላለፉ መልዕክቶችን መቆጣጠርና መገደብ፣
(6)
የተዘረፉ ንብረቶችን ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ በመፈተሽ ለባለቤቶቹ እንዲመለሱ ማድረግ፣
(7)
በትምህርት ተቋማት ሁከትና ረብሻ ተሳትፎ በሚያደርጉ ተማሪዎችና ሰራተኞች ላይ
ህጋዊ እርምት መውሰድ፣ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ ለተቋማቱ ትዕዛዝ መስጠት፣
(8)
ማንኛውም የህዝብን ሰላምና ጸጥታን ሊያደፈርሱ ይችላሉ ወይም ለጉዳት ተጋላጭ
ይሆናሉ ተብለው የሚጠረጠሩና የሚታሰቡ ሰዎችን ወይም ቡድኖችን ወደ ተወሰነ አካባቢ
እንዳይገቡ፣ እንዳይገኙ ወይም በተወሰነ አካባቢ ብቻ እንዲቆዩ ማድረግ እና
(9)
አግባብነት ያላቸውን እርምጃዎችን መውሰድ ይችላል፡፡

አንቀጽ 29. እራስን ለመከላከል በሕግ አስከባሪዎች ስለሚወሰድ እርምጃ
ሕግ አስከባሪዎችናቀ በድርጅቶች ጥበቃ ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች ከላይ የተመለከቱትን ክልከላዎች እንዲሁም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ለማስፈጸምበሚያደርጉት እንቅስቃሴ በጦር መሳሪያ ወይም በስለትና ሕይወታቸውን እና ንብረታቸውን አደጋ ላይ የሚጥል ጥቃት በተሰነዘረባቸው ጊዜእራሳቸውን ለመከላከል የሚያስችላቸውን እርምጃ ሊወስዱ ይችላሉ፡፡

አንቀጽ 30. በትምህርት ተቋማት የመግባት ስልጣን
በትምህርት ቤቶች፣ በዩኒቨርስቲዎች እና በሌሎች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ አድማ የሚያደርጉ ሰዎችን ለመያዝና ችግሩን ለማስቆም የህግአስከባሪ አካላት በእነዚህ ተቋማት ውስጥ በመግባት አስፈላጊውን እርምጃ ለመውሰድ ይችላሉ፣ እንዲሁም በሌሎች የግልና የመንግስት ተቋማትውስጥ አድማ የሚያድርጉ ሰዎችን ለመያዝና ሰላምና ፀጥታ ለማረጋገጥ የሕግ አስከባሪ አካላት ባልደረቦች በእነዚህ ተቋማት ውስጥ ለመግባትእንዲሁም አስፈላጊ ከሆነ ሊቆዩ ይችላሉ፡፡

ክፍል ሶስት
ተሀድሶ እና ፍርድ ቤት ስለማቅረብ

አንቀጽ 31. በሕግ መሰረት በኮማንድ ፖስቱ የሚደረጉ የተሀድሶ እርምጃዎች
(1)
ለፍርድ መቅረብ ያለበትን ፍርድ ቤት እንዲቀርብ ያደርጋል
(2)
ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ በተፈጸሙ ሁከትና የብጥብጥ እንቅስቃሴዎች ላይ በቡድን ወይም በግል የተሳተፈ እና
(
) የጦር መሳሪያ ወይም ማንኛውንም የግልም ሆነ የመንግስት ንብረት የዘረፈ እና በአቅራቢያው ለሚገኝ የህግ አስከባሪ ሀይል የዘረፈውን መሳሪያናንብረት ይህ መመሪያ ከወጣ ጊዜ ጀምሮ 10 ቀናት ውስጥ በአቅራቢያው ላለ ፖሊስ ጣቢያ የመለሰና እጁን የሰጠ ሰው፣
(
) ከዚህ በፊት ለህገ ወጥ ተግባራት የገንዘብና ቁሳቁስ ድጋፍ ያደረገና ይህ መመሪያ በወጣ 10 ቀናት ውስጥ ለፖሊስ ጣቢያ እጁን የሰጠ ሰው፣
(
) ወረቀት በመበተን፣ አድማ በማድረግ የተሳተፈ፣ ያነሳሳ ሰው ይህ መመሪያ በወጣ 10 ቀናት ውስጥ ለፖሊስ ጣቢያ እጁን የሰጠ ሰው፣
(
) ሰው የገደለ፣ ማንኛውንም ንብረት ያቃጠለ፣ ማንኛውንም ወንጀል የፈጸመ ይህ መመሪያ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ 10 ቀናት ውስጥ ለፖሊስጣቢያ እጁን የሰጠ ሰው፣
እንደ የወንጀል ተሳትፎው ቀላልና ከባድነት፣ ዋና ፈፃሚና አባሪ ተባባሪ መሆኑ ታይቶ በኮማንድ ፖስቱ የተሀድሶ ትምህርት ተሰጥቶት እንዲለቀቅይደረጋል፡፡
አዲስ አበባ ጥቅምት 5 ቀን 2009 /
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ኮማንድ ፖስት

PART I: Prohibited Activities
Part 1 A. Activities Prohibited Nationwide
  • Article 1— Agitation and Communication to Incite Violence and Unrest: Covert or overt  agitation and communication that could incite violence and chaos including: printing, preparing and disseminating any content that incites dispute, violence, conflict among people; importing or sending out any publication without prior approval; the exchange of messages via Internet, mobile, text, social media, and radio.
  • Article 2— Communicating with Terrorist Groups: Communicating in any manner with designated terrorist groups or anti-peace forces; storing and disseminating text or storing and promoting emblems of terrorist groups; listening to, watching, or reporting information from Ethiopian Satellite Television, Oromia Media Network, and other terrorist groups outlets is prohibited.
  • Article 3—Unauthorized Demonstrations and Town Hall Meetings: In the interest of protecting the safety and security of citizens, it is prohibited to stage any demonstration and town hall meeting without CP approval.
  • Article 4—Denying the Provision of Public Services: Closing shops and businesses with licenses, or government institutions, or refusing to deliver public services or being absent from work without sufficient reason is prohibited.  Threatening public or private employees from going to work is prohibited.
  • Article 5—Strikes in Educational Institutions: Strikes in any schools, universities, or other higher learning institutions or closing educational institutions or damaging property are prohibited.
  • Article 6—Strikes in Sports Facilities: Inciting unrest, disturbances, and violence in sports venues is prohibited.
  • Article 7—Disrupting Movement of Vehicles: Disrupting the movement of vehicles or pedestrians or other means of transportation by blocking roads or any other means, or increasing transportation fees is prohibited.
  • Article 8—Causing Damage to Infrastructure and Religious Institutions: Causing damage to or looting on private, public, and government property or infrastructure, investments or any other institutions or religious institutions is prohibited.
  • Article 9—Disrupting Public and National Holidays: Disrupting public and national holidays in any way or advancing any political agenda or chanting slogans unrelated to the holiday is prohibited.
  • Article 10—Incitement During Religious, Cultural, and Public Holidays: Inciting in sermons and teachings in religious institutions to induce fear among people or incite conflict is prohibited.
  • Article 11—Disrupting the Functions of Law Enforcement Bodies: Refusing to comply with any order given by law enforcement bodies, disrupting their duties, non-cooperation with searches, or attacking or attempting to attack law enforcement bodies is prohibited.
  • Article 12—Wearing Unauthorized Uniforms: The unauthorized wearing, storing, selling or transferring of official uniforms of law enforcement units is prohibited.
  • Article 13—Firearms or Flammable Materials: Bringing firearms or flammable or sharp materials into market places, religious institutions, or public places is prohibited.
  • Article 14—Transfer of Firearms: Any law enforcement officer or any individual with legally owned firearms is prohibited from transferring the same to a third party.
  • Article 15—Activities That Undermine Tolerance and Unity: Committing acts that undermine tolerance and unity; any attacks based on identity or ethnicity or speech that could incite such attacks is prohibited.
  • Article 16—Undermining National Sovereignty and Security: Any exchange of information or contact by any individual with foreign governments or nongovernmental organizations in a manner that undermines national sovereignty and security; any political party is prohibited from briefing local or foreign journalists in a manner that is anti-constitutional  and undermining sovereignty and security.
  • Article 17—Restricted Areas: Leaving refugee camps without permission from the authorized body or entering the country without visa is prohibited.
  • Article 18—Unauthorized Movement of Diplomats: In the interest of their safety and security, diplomats are prohibited from traveling no farther than 40 km outside of Addis without prior notification to and approval from the CP.
  • Article 19—Duty of Law Enforcement Officers: Any law enforcement officer is prohibited from resigning from their job or take leave during the SOE unless and otherwise forced by a situation.
  • Article 20—Contributing to Public Unrest and Instability: Providing, money, materials, shelter, encouragement, or any other support to those who commit illegal activities is prohibited. 
PART I: Prohibited Activities 
Part1 B. Restrictions in Specific Parts of the Country 
  • Article 21—Mobility with Firearms: Any firearms, sharp materials, or flammable items that could be used as a weapon may not be taken outside one’s home.
  • Article 22— Attacks Targeting Infrastructure and Economic Interests: Unauthorized persons are forbidden to be in the vicinity of economic interests, infrastructure, investments, industrial areas, and commercial farms from 6:00 pm to 6:00 am; law enforcement bodies are authorized to take any necessary actions against violators.
  • Article 23—Curfew: Any individual is not allowed to move from place to place violating curfews imposed by the CP in a specific location and time.
  • Article 24— Disrupting Efforts to Control Violence: It is prohibited to violate orders given to individuals or groups suspected of posing a threat, groups vulnerable to harm (who may be ordered to stay away from certain areas or buildings or to stay within certain areas); it is prohibited to enter a road blocked by the order of CP.
PART I: Prohibited Activities
Part I C. Providing Information and Notifying Authorities 
  • Article 25—Documenting rental units: Any person who rents out a house, room, place, vehicle, or similar item is required to document information about the identity of the renter and should report to police within 24 hours; in the case of a foreign national renter, the owner should make a copy of the passport and rental agreement and must report to a nearby police station. 
  • Article 26—Obligation to provide information: For the safety and security of the public, all organizations are required to give information when asked by law enforcement bodies at all levels.
            PART II: Power To Implement Measures
  • Article 27—Law enforcement bodies are authorized to take emergency action against: Any person or organization that violates prohibitions under articles 1-24.  (Note: it is not clear how the emergency actions are different from those authorized under article 28.)
  • Article 28—Consequences for violations of Part 1 (Articles 1-26): Individuals may be arrested without a court order and may be held at a location determined by the CP for a term up to the end of the SOE; detainees may be eligible for release after completing a rehabilitation program or will face trial based on the severity of their crime; law enforcement or the CP may censor any message transmitted by radio, television, video, text, image, theater, or film that violates the prohibitions listed in Part 1; authorities may confiscate and return to the original owner, any looted property discovered through the search of a suspected violator's house without a court order; authorities may take legal measures or order educational institutions to take measures against any student or staff member who violates the prohibitions in Part 1; any group(s) or individual(s) suspected of posing a threat to public peace and security or individuals or groups assumed to be vulnerable to harm can be prohibited from entering certain areas or may be confined within restricted areas; authorities may take other relevant measures.
  • Article 29—Authorization for law enforcement to exercise self-defense: law enforcement bodies and individuals engaged in protection duties may take any defensive measures necessary if attacked by firearms or sharp materials.
  • Article 30—Authority for law enforcement to enter into educational institutions: Law enforcement bodies may enter schools, universities, and other related institutions and can take measures to control strikes or protests; in addition to educational institutions, authorities may enter and occupy public and private organizations if necessary to arrest and control strikes or protesters.  They may stay inside these institutions whenever necessary.
PART III: Rehabilitation Measures
  • Article 31—Rehabilitation measures: The CP will bring to justice those who deserve it. Individuals or groups who were involved in conducting violence during the last year, upon returning looted property, including government firearms and private property to nearby police stations within 10 days of this announcement may receive rehabilitation as punishment; those who supported illegal activities materially or financially and surrender to the nearby police station within 10 days of this announcement may receive rehabilitation as punishment; anyone who was involved in protest by distributing materials, involved in murder, or destruction of property may turn themselves into police within 10 days of the enactment of this law; the duration of rehabilitation depends on the severity of the crime; individuals may be set free after undergoing rehabilitation programs.  (Note: It remains unclear whether the SOE and accompanying articles have been enacted by decree or must still be approved by parliament.)

Ethiopia Travel Warning

Last Updated: October 21, 2016 
The U.S. Department of State warns U.S. citizens to defer all non-essential travel to Ethiopia due to ongoing unrest that has led to hundreds of deaths, thousands of arrests, as well as injuries and extensive property damage, especially in Amhara and Oromia States. The U.S. Embassy’s ability to provide consular services in many parts of the country is limited by the current security situation.
The Government of Ethiopia declared a State of Emergency effective October 8, 2016. An October 15 decree states that individuals may be arrested without a court order for activities they may otherwise consider routine, such as communication, consumption of media, attending gatherings, engaging with certain foreign governments or organizations, and violating curfews. The decree prohibits U.S. and other foreign diplomats from traveling farther than 40 kilometers outside of Addis Ababa without prior approval from the Government of Ethiopia, which severely affects the U.S. Embassy’s ability to assist U.S. citizens. The full text of the decree implementing the State of Emergency is available on the U.S. Embassy’s website.
Internet, cellular data, and phone services have been periodically restricted or shut down throughout the country, impeding the U.S. Embassy’s ability to communicate with U.S. citizens in Ethiopia. You should have alternate communication plans in place, and let your family and friends know this may be an issue while you are in Ethiopia. See the information below on how to register with the U.S. Embassy to receive security messages.
Avoid demonstrations and large gatherings, continuously assess your surroundings, and evaluate your personal level of safety. Remember that the government may use force and live fire in response to demonstrations, and that even gatherings intended to be peaceful can be met with a violent response or turn violent without warning. U.S. citizens in Ethiopia should monitor their security situation and have contingency plans in place in case you need to depart suddenly.
U.S. government personnel are restricted from personal travel to many regions in Ethiopia, including Oromia, Amhara, Somali and Gambella states, southern Ethiopia near the Ethiopian/Kenyan border, and the area near the Ethiopia/Eritrea border. Work-related travel is being approved on a case-by-case basis. U.S. government personnel may travel to and within Addis Ababa without restrictions. For additional information related to the regional al-Shabaab threat, banditry, and other security concerns, see the Safety and Security section of the Country Specific Information for Ethiopia.
Due to the unpredictability of communication in the country, the Department of State strongly advises U.S. citizens to register your mobile number with the U.S. Embassy to receive security information via text or SMS, in addition to enrolling in the Smart Traveler Enrollment Program (STEP).

Saturday, October 15, 2016

What is አንቀጽ 93?





አንቀጽ 93
ሀ/ የውጭ ወረራ ሲያጋጥም ወይም ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን አደጋ ላይ የሚጥል ሁኔታ ሲከሰትና በተለመደው የሕግ ማስከበር ሥርዓት ለመቋቋም የማይቻል ሲሆን፣ ማናቸውም የተፈጥሮ አደጋ ሲያጋጥም ወይም የሕዝብን ጤንነት አደጋ ላይ የሚጥል በሽታ ሲከሰት፣ የፌዴራሉ መንግሥት የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመደንገግ ሥልጣን አለው፡፡
ለ/ የተፈጥሮ አደጋ ሲያጋጥም ወይም የሕዝብን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል በሽታ ሲከሰት የክልል መስተዳድሮች በክልላቸው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሊያውጁ ይችላሉ፡፡ዝርዝሩ ክልሎች ይህን ሕገ መንግሥት መሰረት በማድረግ በሚያወጧቸው ሕገመንግሥቶች ይወሰናል፡፡
በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 /ሀ/ መሰረት የሚታወጅ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ፣
ሀ/ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሥራ ላይ ባለ ጊዜ የታወጀ ከሆነ በታወጀ በአርባ ስምንት ሰዓታት ውስጥ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረብ አለበት አዋጁ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሁለት ሦስተኛው ድምጽ ተቀባይነት ካላገኘ ወዲያውኑ ይሻራል፡፡
ለ/ ከላይ በንዑስ አንቀጽ /ሀ/ ሥር የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሥራ ላይ ባልሆነበት ወቅት የሚታወጅ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረብ ያለበት አዋጁ በታወጀ በአሥራ አምሥት ቀናት ውስጥ ነው፡፡
በሚኒስትሮች ምክር ቤት የተደነገገው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በምክር ቤቱ ተቀባይነት ካገኘ በኝላ ሊቆይ የሚችለው እስከ ስድስት ወራት ነው፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሁለት ሦስተኛ ድምጽ አንድን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በየአራት ወሩ በተደጋጋሚ እንዲታደስ ሊያደርግ ይችላል፡፡
ሀ/ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በሚታወጅበት ጊዜ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚያወጣቸው ደንቦች መሰረት የሀገርን ሰላምና ሕልውና፣ የሕዝብን ደህንነት፣ሕግና ሥርዓትን የማስከበር ሥልጣን ይኖረዋል፡፡
ለ/ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሥልጣን በሕገ መንግሥቱ የተቀመጡትን መሰረታዊ የፖለቲካና የዴሞክራሲ መብቶችን፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ለማወጅ ምክንያት የሆነውን ጉዳይ ለማስወገድ ተፈላጊ ሆኖ በተገኘውደረጃ፣ እስከ ማገድ ሊደርስ የሚችል ነው፡፡
ሐ/ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሥራ የሚያወጣቸው ድንጋጌዎችና የሚወስዳቸው እርምጃዎች በማናቸውም ረገድ በዚህ ሕገመንግሥት አንቀጽ 1፣፣ 88፣ 25፣ እና 39 ንዑስ አንቀጽ 1 እና 2 የተቀመጡትን መብቶች የሚገድቡ ሊሆኑ አይችሉም፡፡
በሀገሪቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በሚታወጅበት ወቅት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከአባላቱና ከሕግ ባለሙያዎች መርጦ የሚመድባቸው ሰባት አባላት ያሉት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም መርማሪ ቦርድ ያቋቁማል፡፡ ቦርዱ አዋጁ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሚጸድቅበት ጊዜ ይቋቋማል፣
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም መርማሪ ቦርድ የሚከተሉት ሥልጣንና ኃላፊነቶች አሉት፡፡
ሀ/ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት የታሰሩትን ግለሰቦች ስም በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ይፋ ማድረግና የታሰሩበትን ምክንያት መግለጽ፣
ለ/ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ወቅት የሚወሰዱት እርምጃዎች በማናቸውም ረገድ ኢሰብዓዊ አለመሆናቸውን መቆጣጠርና መከታተል፣
ሐ/ ማናቸውም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እርምጃ ኢሰብዓዊ መሆኑን ሲያምንበት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወይም የሚኒስሮች ምክር ቤት እርምጃውን እንዲያስተካክል ሐሳብ መስጠት፣
መ/ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እርምጃዎች ኢሰብዓዊ ድርጊት የሚፈጽሙትን ሁሉ ለፍርድ እንዲቀርቡ ማድረግ፣
ሠ/ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲቀጥል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥያቄ ሲቀርብ ያለውን አስተያየት ለምክር ቤቱ ማቅረብ፡፡



Details of the Ethiopian State of Emergency announced

We have breaking news. The Ethiopian State of Emergency Detail is out. The Amharic version is very detail but hard to read. As soon as it is ready we will post it.



Details of the State of Emergency announced
Details of the State of Emergency was announced by Siraj Fegessa Minister of Defence and Secretariat of the Command Post on Saturday December 15.

The details include travel ban and a curfew on investments, major projects and governmental institutions.
Here are the major points
According to the details Diplomats of other Nations cannot go outside of Addis Ababa city on a 40 Kilometer radius. It is stated that the ban is said to be for their own security.

Moreover 50 kilometers from borders inside the country is now a red zone and anyone cannot carry a firearm even if it is legal or any other inflammable things on this red zone. The red zone also includes the country’s major roads that connect to neighboring countries. The side of the roads to the tune of 25 kilometers on both sides are classified as red zones, according to the secretariat. These roads include the Addis-Djibouti, Addis-Shashamane-Moyale, Addis-Shashamane-Dolo, Addis-Assosa, Addis – Harar, Addis – Gambela, Addis Gebreguracha, Gondar-Metema, and Gondar-Humera.
A curfew was also imposed on major projects, factories, farms and governmental institution that runs from dusk to dawn. The announcement said that anyone cannot enter these institutions after 6 pm and before 6 am. If anyone violates these rules, security forces are ordered to take the necessary measures.


All political parties are also banned from giving press statements that incites violence.
 




The details also states that no one including religious leaders cannot make political statements on religious gatherings, national, and sportive festivities.

Educational institutions are also included in the details. The directive states that it is banned to demonstrate in educational institutions.


Security forces are also banned to ask for a leave and cannot also resign from their position.


It is also banned to communicate with outside forces using any means of communication including Facebook or any other social media.
Refugees cannot also leave their camp without proper authorization.
It is also illegal now to watch TV stations such as ESAT and OMN and other radio stations.
No one cannot shut down licensed businesses.


















በማንኛውን የሀገሪተሩ ክፍል የተከለከሉ ተግባራት
ማንኛውን ሁከት እና ብጥብጥና በህዝቦች መካከል መጠራጠር እና መቃቃር የሚፈጥር ይፋዊም ሆነ ድብቅ ቅስቀሳ በማናቸውም መልኩ እና ዘዴ ማድረግ፤ ፅሁፍ ማዘጋጀት ማተምና ማሰራጨት፣ ትእይንት ማሳየት፣ በምልክት መግለፅ ወይም መልእክትን በማናቸውም ሌላ መንገድ ለህዝብበ ይፋ ማድረግ ፈቃድ ሳይኖር በማንኛውም ህትመት ወደ ሀገር ወስጥ ማስገባት ወይም ወደ ውጪ ሀገር መላክ በመመሪያው ተከልክሏል።
መልእክት በኢንተርኔት፣ በሞባይል በጽሁፍ፣ በቴሌቭዠን፣ በሬድዮ፣ በማህበራዊ ሚድያ ወይም በሌሎች የግንኙነት ዘዴዎች መለዋወጥም በመመሪያው ተከለከለ ተግባር ነው።
ከሽብርተኛ ቡድኖች ጋር ግንኙነት ማድርግ
በሽብርተኝነት ከተሰየሙ ድርጅቶች እና ከፀረ ሰላም ሃይሎች ቡድኖች ጋር ማንኛውንም ግንኙነት ማድረግ፤ የአሸባሪ ድርጅቶች የተለያዩ ፅሁፎችን ማሰራጨት፣ አርማቸውን መያዝ ወይም ማስተዋወቅ፣ የቴሌቭዥን ወይም የሬድዮ ፕሮግራሞችን መከታተል፣ የኢሳት፣ ኦ ኤም ኤን እና የመሳሰሉትን የሽብርተኛ ድርጅቶች ሚድያዎች ማሳየት፣ መከታተል እና ሪፖርት ማድረግ የተከለከለ ነው።
ያልተፈቀደ ሰልፍ እና የአደባባይ ስብስባ
የህዝብና የዜጎች ሰላምና ፀጥታ ለማስጠበቅ ሲባል ከኮማንድ ፖስቱ ፈቃድ ውጪ ማንኛቸውንም ሰልፍ እና የአደባበይ ስብስባ ማድረግ ከተከለከሉ ተግባራት ውስጥ አንዱ ነው።
ለህዝብ አገልግሎት አለመስጠት
በመመሪያው እንደ ተደነገገው ህዝብ የሚጠቀምባቸውን ወይም ፈቃድ የወጣባቸው የንግድ ስራዎች፣ ሱቆች፣ ወይም የመንግስት ተቋማት መዝጋት ወይም ምርት እና አገልግልት ማቋረጥ፣ ከስራ ቦታ ያለበቂ ምክንያት መጥፋት ወይም ስራ ማቆም፣ ተገቢውን አገልግሎት አለመስጠት እና ስራ መበደል ክልክል ነው።
የመንግስት ወይም የግል ተቋማት ሰራተኞች ወደ መደበኛ ስራቸው እንዳይገቡ መዛት እና ማስፈራራትም ተከልክሏል።
በትምህርት ተቋማት አድማ ማድረግ ከተከለከሉ ተግባራት መካከል የሚጠቀስ ነው።
መመሪያው በትምህርት ቤቶች፣ በዩንቨርስቲዎች፣ እና በሌሎች የከፍትኛ ትምህርት ተቋማት የመማር ማስተማር ሂደትን የሚያውክ አድማ ማድረግ፣ የትምህርት ተቋማትን መዝጋት ወይም በነዚህ ተቋማት ላይ ጉዳት ማድረስ የተከለከለ መሆኑ ተመላክቷል።
በስፖርት ማዘውተሪያ አድማ ማድግም የተከለከለ ሌላው ተግባር ሲሆን፥ መመሪያው ላይ እንደሰፈረው በስፖርት ማዘውተሪያ ማእከላት፣ ከስፖርታዊ ጨዋነት ውጪ የሆኑ ሁከቶችን፣ ብጥብጦችን መፍጠር የተከለከለ መሆኑ ተደንግጓል።
የተሸከርካሪዎችን እንቅስቃሴ ማወክ
መመሪያው የተሽከርካሪ፣ የእግረኛ እና ሌሎች የመጓጓዣ ዘዴዎችን እንቅስቃሴ መንገድ በመዝጋት በዛቻ እና በሌሎች መሰል ድርጊቶች ሰላማዊ እንቅስቃሴን ማወክ፣ አገልግሎት ማስተጓጎል፣ የመጓጓዣ ዋጋ ታሪፍ መጨመር፣ የሚመለከተው አካል ከደለደለደው የስራ ስምሪት ውጪ መሆንን መመሪያው ይከለክላል።
በመሰረተ ልማት አውታሮች እና ሃይማኖታዊ ተቋማት ላይ ጉዳት ማድርሰም በመመሪያው ተከልክሏል።
በግል፣ በህዝብ እና በመንግስት ማናቸውም ተቋማት፣ መሰረተ ልማቶች፣ በኢንቨስትመንት እና በሌሎች የልማት አውታሮች እንዲሁም ሃይማኖታዊ ተቋማት ላይ በማንኛውንም ምንገድ ጉዳት ማድረስ ወይም ዘረፋ መጸፈምም የተከለከለ ነው ይላል መመሪያው።
ህዝባዊ እና ብሄራዊ በዓላትን ማወክን አስመልክቶ በመመሪያው የሰፈረው ድንጋጌውም፣ በኣላቱን በማንኛውም ሁኔታ ማወክ፣ ማደናቀፍ፣ ወይም ከበዓሉ አላማ ጋር የማይገናኙ፣ የፖለቲካ አጀንዳዎች ወይም መፈክሮችን በማንኛውም መንገድ ማስተጋባትን ይከለክላል።
በሃይማኖታዊ ፣ባህላዊ እና ህዝባዊ በኣላት ላይ ቅስቀሳ ማደረግ
በመመሪያው መሰረት በሃይማኖታዊ ተቋማት ውስጥ በሚደረጉ ስብከቶች እና ትምህርቶች ሃይማኖታዊ አስተምህሮ ከማስተማር ውጪ በህዝቦች መካከል መጠራጠር እና መቃቃርን የሚፈጥር፣ በህብረተሰቡ ላይ ስጋት የሚፈጥር፣ ሁከት እና ብጥብጥ የሚቀሰቅስ ቅስቀሳ ማደረግ ተከልክሏል።
የህግ አስከባሪዎችን ስራ ስለ ማወክም መመሪያው ያስቀመጣቸው ክልከላዎች
የህግ አስከባሪ አካላት የሚሰጡትን ማንኛውንም ትእዛዝ አለማክበር ስራቸውን ማደናቀፍ፣ ለፍተሻ አለመተባበር ወይም እንዲቆም ሲጠየቅ አለመቆም፣ ኬላዎችን ጥሶ ማለፍ ከተከለከሉ ተግባራት ውስጥ የሚጠቀሱ ናቸው።
በህግ አስከባሪ አካላት ባልደረቦች ላይ ጥቃት መፈፀም ወይም ለመፈፀም መሞከር የተከለከለ ሌላ ተግባር ነው።
ያልተፈቀዱ አልባሳትን ስለ መለስበስም 
የህግ አስከባሪ ሃይሎችን የደንብ ልብስ (ዩኒፎርም) መልበስ፣ ይዞ መገኘት፣ ቤት ማስቀመጥ፣ አሳልፎ መስጠት እና መሽጥ ክልክል መሆኑም በመመሪያው ተደንግጓል።
ማናቸውም የጦር መሳሪያ፣ ስለት ወይም እሳት የሚያስነሱ ነገሮችን ወደ ገበያ፣ ሀይማኖት ተቋማት፣ ህዝባዊ በዓላት የሚከበሩበት ወይም ወደ ማናቸውም ህዝብ የሚሰበሰብበት ቦታ ይዞ መግባት የተከለከለ ነው።
ማንኛውም የህግ አስከባሪ አካላት ባልደረባ ወይም ማንኛውም ህጋዊ ትጥቅ ያለው ሰው ትጥቁን በማንኛውም ሁኔታ በሶስተኛ ሰው እጅ እንዲገባ ማድረግም የተከለከለ ነው።
ማንነትን ወይም ዘረን መሰረት ያደረገ ማንኛውም አይነት ጥቃት መፈፀም ወይም ጥቃት አንዲፈፀም የሚያነሳሳ ንግግር መናገርንም መመሪያው ይከለክላል።
ማንኛውም ሰው ከውጭ መንግስታትም ሆነ ከውጭ ማንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር የሀገር ሉአላዊነት፣ ደህንነት እና ህገ መንግስታዊ ስርዓትን ሊጎዳ የሚችል ግንኙነት እና የመልእክት ልውውጥ ማድረግም በመመሪያው የተከለከለ ነው።
እንዲሁም ማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ የሀገርን ሉአላዊነት፣ ደህንነት እና ህገመንግስታዊ ሰርዓትን የሚጎዳ ማናቸውም ጋዜጣዊ መግለጫ ለሀገር ውስጥም ሆነ ለውጭ ሚዲያዎች መስጠጥም መመሪያው ከልክሏል።
ያልተፈቀደ ቦታ ከመገኘት ጋር ተያይዞም መመሪያው፥ ከስደተኛ ካምፕ አግባብ ካለው አካል ከሚሰጥ ፈቃድ ውጪ መውጣት ወይም ህጋዊ ቪዛ ሳይኖረው ወደ ሀገር ወስጥ መግባት ክልክል ነው።
ከኮማንድ ፖስቶ እውቅና እና ፈቃድ ሳያገኙ ዲፕሎማቶች ለራሳቸው ደህንነት ጥበቃ ሲባል ከአዲስ አበባ 40 ኪሎ ሜትር ራዲየስ ውጪ መንቀሳቀስ የተከለከለ መሆኑም በመመሪያው ላይ ተብራርቷል።
የህግ አስከባሪን በተመለከተም ማንኛውም የህግ አስከባሪ አካል ባልደረባ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተፈጻሚ በሚሆንበት ጊዜ ከስራ መልቀቅ ወይም አስገዳጅ ሁኔታ ካልተፈጠረ በስተቀር የዓመት እረፍት ፈቃድ መውሰድንም መመሪያው ይከክላል ተብሏል።
በመመሪያው የተከለከሉ ተግባራትን በማለፍ ህገ ወጥ ድርጊት የሚፈጽሙ ሰዎችን፣ በገንዘብ እና በቁሳቁስ ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ መደገፍ እንዲሁም ከለላ መስጠት፣ መደለያ መስጠት እና ማበረታታትንም መመሪያው እንደሚከለክል ተነግሯል።
በተወሰኑ አካባቢዎች እንዳይፈጸሙ የተከለከሉ ተግባራት

ኮማንድ ፖስቱ እየወሰነ ይፋ በሚያደርጋቸው ቦታዎች ወይም አካባቢዎች ላይ ማናቸውነም የጦር መሳሪያ፣ ስለት፣ ወይም እሳት የሚያስነሱ ነገሮችን ከግቢውና ይዞታው ውጪ ይዞ መንቀሳቀስ ክልክል መሆኑ በመመሪያው ላይ ተገልጿል።

የሰዓት እላፊን በተመለከተ

የኢኮኖሚ አውታሮች፣ መሰረተ ልማትና የኢንቨስትመንት ተቋማት፣ የእርሻ ልማቶች፣ ፋብሪካዎችና መሰል የልማት ተቋማት አካባቢ ከቀኑ 12 ሰዓት በኋላ እስከ ንጋት 12 ሰዓት ድረስ ከተፈቀደለት ሰራተኛ በስተቀር ማንኛውም ሌላ ሰው መንቀሳቀስንም መመሪያው ይከለክላል።

በእነዚህ ስፍራዎች ላይ የሰዓት እላፊውን ተላልፎ በተገኘ ማንኛውም ሰው ላይ የጥበቃ ወይም የህግ አስከባሪ አካላት አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስዱ ስልጣን እንደተሰጣቸውም ተብራርቷል።

የሰዓት እላፊን በተመለከተም ማናቸውም ሰው በኮማንድ ፖስቱ ውሳኔ የሰዓት እላፊ በይፋ በሚገለጽበት ቦታና ጊዜ የሰዓት እላፊ ክልከላን በመተላላፍ ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ አንደማይፈቀድም ተገልጿል።
በተያያዘ ሰላምና ፀጥታን ሊያደፈርሱ ይችላሉ ተብለው የሚጠረጠሩ ሰዎች ወይም ቡድኖች ወይም ለጉዳት ተጋላጭ ናቸው ተብለው የሚገመቱ ሰዎች ወይም ቡድኖች ወደ ተወሰነ አካባቢ ወይም ህንፃ እንዳይገቡ ወይም በተፈቀደላቸው አንድ የተወሰነ አካባቢ ብቻ እንዲቆዩ የተሰጠን ትእዛዝ መተላለፍ ክልክል መሆኑም ተገልጿል።

ለአካባቢው ደህንነት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት ወደ ተዘጋ መንገድ ማንም ሰው እንዳይገባ በኮማንድ ፖስቱ የተሰጠውን እድግ ወይም ክልከላ መተላለፍም መመሪያው ይከለክላል።

መረጃ የመስጠት እና የማስታወቅ ግዴታን በተመለከተ

ማኛውም ቤት፣ ቦታ፣ ክፍል ወይም ተሽከርካሪ ወይም ተመሳሳይ መገልገያዎችን አከራይ ከሆነ የተከራዩን ማንነት በዝርዝርና በጽሁፍ የመያዝ እና አቅራቢያው ላለ ፖሊስ ጣቢያ በ24 ሰዓት ወስጥ የማሳወቅ ግዴታ አለበት፤ በተጨማሪም የውጭ ሀገር ዜጋን ያከራየ እንሆነ የፓስፖርቱን ኮፒ እና የኪራዩን ውል በአቅራቢያው ላለ ፖሊስ ጣቢያ የማሳወቅ ግዴታ አለበት።

የህዝብ ሰላምና ፀጥታን ለማስጠበቅ ሲባል ማንኛውም ተቋም መረጃ እንዲሰጥ በየደረጃው ባለ የህግ አስከባሪ አካል ሲጠየቅ የመስጠት እና የመተባበር ግዴታ አለበት።
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) እርምጃ ለመውሰድ ስልጣን ስላለው ሰው በተደነገገበት የመመሪያው ክፍል፤ የህግ አስከባሪዎች የመመሪያውን ድንጋጌ ተላልፈው በተገኙ ድርጅቶች እና ግለሰቦች ላይ ቀጥሎ የተዘረዘሩትን እርምጃዎች መውሰድ እንደሚችሉ ተመላክቷል።
ክልከላዎች ሲጣሱ የሚወሰዱ እርምጃዎችን በተመለከተ፤ በመመሪያው የተከለከሉ ተግባራት ተፈፅመው ሲገኙ፤
1. ህግ አስከባሪዎች ተጠርጣሪዎችን ያለ ፍርድ ቤት ትእዛዝ በቁጥጥር ስር ማዋል ይችላሉ፤

2 አዋጁ ተፈፃሚነቱ እስከሚያበቃበት ድረስ ኮማንድ ፖስቱ በሚወስነው ቦታ እንዲቆዩ የማድረግ፤

3 ተገቢውን የተሃድሶ ትምህርት በመስጠት የሚለቀቀውን እንዲለቀቅ፣ ወደ ፍርድ ቤት የሚቀርበውን ደግሞ እንዲቀርብ ማደረግ

4 ያለፍርድ ቤት ትእዛዝ በማንኛውም ስአት ብርበራ የማድርግ፤ የአካባቢውን ህዘብ እና ፖሊስ በማሳተፍ ማንኛውንም ወንጀል የተፈፀመበት ወይም ሊፈፀምበት የሚችል ንብረት መያዝ፤ወይም ንበረቱ እንዲጠበቅ ማደረግ

5 በማንኛውም ሬድዮ ቴሌቭዠን ድምፅ፣ ምስል ፎቶ ግራፍ፣ ቲያትር እና ፊልም የሚተላለፉ መልእክቶችን መቆጣጠር እና መገደብ

6 የተዘረፉ ንብረቶችን ያለፍርድ ቤት ትእዛዝ በመፈተሽ ለባለቤቶቹ እንዲመለሱ ማድረግ

7 በትምህርት ተቋማት ሁከት እና ረብሻ ተሳትፎ በሚያደርጉ ተማሪዎች እና ሰራተኞች ላይ ህጋዊ እርምት መውሰድ እና አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ ለተቋማቱ ትእዛዝ መስጠት

8 ማንኛውም የህዝብን ሰላም እና ፀጥታ ሊያደፈርሱ ይችላሉ ወይም ለጉዳት ተጋላጭ ይሆናሉ ተብለው የሚጠረጠሩ እና የሚታሰቡ ሰዎችን እንዲሁም ቡድኖችን ወደ ተወሰነ አካባቢ እንደይገቡ፣ እንዳይገኙ ወይም በተወሰነ አካባቢ ብቻ እንዲቆዩ ማድረግን ጨምሮ አግባብነት ያለቸውን እርምጃዎችን መውሰድ ይችላል።

ራስን ለመከላከል በፀጥታ ሀይልች ስለሚወሰድ እርምጃም መመሪያው ድንጋጌዎችን አስቀምጧል።

ህግ አስከባሪዎች እና በድርጅት ጥበቃ ላይ የተሰማሩ ሰዎች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ለማስፈፀም በሚያደርጉት እንቅስቃሴ በጦር መሳሪያ ወይም በስለት ህይወታቸውን እና ንብረተቻውን አደጋ ላይ የሚጥል ጥቃት በተሰነዘረ ጊዜ ራሳቸውን ለመከላከል የሚያስችላቸውን እርምጃ ሊወስዱ ይችላሉ።

በትምህርት ተቋማት የመግባት ስልጣንም በመመሪያው ስንጋጌ ወጥቶለታል። መመሪያው እንደሚለው በትምህርት ቤቶች እና በሌሎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ አድማ የሚያደርጉ ሰዎችን ለመያዝ እና ችግሩን ለማስቆም የህግ አስከባሪ አካላት በተቋማቱ ውስውጥ በመግባት አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ ይችላሉ።

በሌሎች የመንግስት እና የግል ተቋማት አድማ የሚያደርጉ ሰዎችን ለመያዝ እና ሰላም እና ፀጥታ ለማረጋገጥ የህግ አስከባሪ አካላት እና ባልደረቦች በተቋማቱ ውስጥ ለመግባት እና አስፈላጊ ከሆነ ለማቆየት ይችላሉ።

ተሃድሶ እና ፍርድ ቤት ማቅረብን በተመለከተም መመሪያው ይህንን ይላል፤ 
በህግ መሰረት በኮማንድ ፖስቱ የሚደረግ የተሃድሶ እርምጃዎች እንደሚኖሩ በተጠቀሰበት የአዋጁ ድንጋጌ፤ ኮማንድ ፖስቱ ለፍርድ መቅረብ ያለበትን እንዲቀርብ ያደርጋል፤
ባለፈው አንድ አመት ውስጥ በተፈፀሙ የሁከት እና የነውጥ እንቅስቃሴዎች ላይ በቡድን ወይም በግል የተሳተፈ

የጦር መሳሪያ ሳይዝ የመንግስትም ሆነ የግለሰን ንብረት የዘረፈ እና በአቅራቢያው ለሚገኝ ፀጥታ አስከባሪ ሃይል የዘረፈውን መሳሪያ እና ንብረት፤ ይህ መመሪያ ከወጣ በኋላ ባሉት አስር ቀናት ውስጥ በአቅራቢያው ላለ ፖሊስ ጣቢያ የመለሰ እና እጁን የሰጠ ፤

ከዚህ በፊት ለህገ ወጥ ተግባራት የገንዘብ እና የቁሳቁስ ድጋፍ ያደረገ፣ወረቀት በመበተን፣ አድማ በማድርግ የተሳተፈ እና ያነሰሳ፣ ሰው የገደለ፣ማንኛውንም ንብረት ያቃጠለ፣ማንኛውንም ወንጀል የፈፀመ ስው፤
ይህ መመሪያ ከወጣ በኋላ ባሉት 10 ቀናት ውስጥ በአቅራቢያው ላለ ፖሊስ ጣቢያ የመለሰ እና እጁን ከሰጠ እንደ የወንጀል ተሳትፎው ቀላል እና ከባድነት ዋና ፈፃሚ እና አባሪ ተባባሪ መሆኑ ታይቶ፣ በኮማንድ ፖስቱ የተሃድሶ ትምህርት ተሰጥቶት እንዲለቀቅ ይደረጋል።
ዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተቀመጠ በተወሰኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች እንዳይፈጸሙ የተከለከሉ ተግባራት ተፈጻሚ የሞሆኑባቸው ስፍራዎች ኮማንድ ፖስቱ ይፋ አድርጓል።
እነዚህም ከድንበሮች 50 ኪሎ ሜትር ገባ ብሎ ያሉ ስፍራዎች ቀይ ዞን ተብሎ በመመሪያው ላይ ተለይተዋል።
በነዚህ ስፍራዎች የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ፣በልማት አውታሮች እና በመሰረተ ልማቶች ላይ ጥቃት መሰንዘር እና ሁከትን ለማስቆም እና አደጋን ለመከላከል የሚደረግ እንቅስቃሴን ማወክ የሚሉት ክልከላዎች ተግባራዊ ይሆናሉ።
እንዲሁም በዋና ዋና የሀገሪቱ መንገዶች ማለትም፥ ከአዲስ አበባ ጅቡቲ፣ ከአዲስ አበባ ሻሸመኔ ዶሎ፣ ከአዲስ አበባ ሀረር፣ ከአዲስ አበባ አሶሳ፣ ከአዲስ አበባ ጋምቤላ፣ ከአዲስ አበባ ገብረ ጉራቻ፣ ከጎንደር መተማ፣ ከጎንደር ሁመራ፣ ከአዲስ አበባ ሻሸመኔ ሞያሌ 25 ሜትር ወደ ቀኝ እና 25 ሜትር ወደ ግራ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ፣ በልማት አውታሮች እና በመሰረተ ልማቶች ላይ ጥቃት መሰንዘር እና ሁከትን ለማስቆም እና አደጋን ለመከላከል የመኒደረግ እንቅስቃሴን ማወክ አይቻልም።
ቀይ ዞን ተብለው የተለዩት አካባቢዎች በሀገሪቱ የተወሰኑ አካባቢዎች እንዳይፈጸሙ የተከለከሉ ተግባራት የሚተገበሩባቸው ናቸው።


Friday, October 14, 2016

Kurt.. The best raw steak ever






Raw meat, a manly dish in Ethiopia. Raw meat dishes are served in Ethiopian restaurants in the U.S. ... In Ethiopia, Solomon says, eating raw meat tends to be a "male thing" that guys might do together.


Why Do Ethiopians Eat So Much Raw Meat? | Washington City Paper
Oct 2, 2009 - Kitfo, of course, isn't the only raw meat offered in Ethiopian cooking (or non-cooking). There's also tere saga, sometimes known as kurt, but that ...






Tuesday, October 11, 2016

ዩናይትድ ስቴትስ በኢትዮጵያ ጉዳይ ሥጋቷን ገለፀች (VOA)

ጃን ኪርቢ - የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ቃል አቀባይጃን ኪርቢ - የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ቃል አቀባይ
የዩናይትድ ስቴትስ ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው የውጥረት ሁኔታ ሥጋት ያደረባት መሆኑን የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቷ ቃል አቀባይ ጃን ኪርቢ ዛሬ ከአሜሪካ ድምፅ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት መልስ አስታውቀዋል፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው የውጥረት ሁኔታ ሥጋት ያደረባት መሆኑን የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቷ ቃል አቀባይ ጃን ኪርቢ ዛሬ ከአሜሪካ ድምፅ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት መልስ አስታውቀዋል፡፡
በኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች ላነሷቸው የመሬት መብትና የምርጫ ሕግን ማሻሻያ የመሳሰሉ ብሦቶች መልስ ለመስጠት መንግሥት ቃል መግባቱን ፕሬዚዳንት ሙላቱ መስከረም 20 ለፓርላማው ያደረጉትን ንግግር መንግሥታቸው እንዳጤነው ቃል አቀባዩ ገልፀው የኢትዮጵያ መንግሥት ያቀረባቸውን ሃሣቦች ተግባራዊ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንዲንቀሣቀስ እንደሚያበረታታ አመልክተዋል፡፡
ኪርቢ በማከልም የኢትዮጵያ መንግሥት ባለፈው ሣምንት መጨረሻ ላይ የደነገገውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ፤ በተለይም ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰዎችን መያዝን፣ ነፃ ሃሣብን መገደብን፣ ሕዝባዊ ስብሰባዎችን ማገድን እና የሰዓት ዕላፊ ገደብ መጣልን የመሳሰሉ የአስቸኳይ ጊዜ እርምጃዎቹን ተግባራዊ ለማድረግ የሚፈልግበትን ሁኔታ ግልፅ እንዲያደርግ መንግሥታቸው እንደሚፈልግም አስረድተዋል፡፡
“እነዚህ እርምጃዎች ሥርዓትን ለመመለስ የታሰቡ ቢሆኑ እንኳ - አሉ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ ጃን ኪርቢ - ነፃ ድምፆችን ማፈንና በኢትዮጵያዊያን መብቶች ውስጥ እራስን የሚጎዳ ጣልቃ ገብነት ማድረግ ለብሦቶቹ መፍትኄ ከማግኘት ይልቅ ሁኔታዎችን የሚያባብሱ ነው የሚሆኑት፡፡”