የቦ ታክስ

ለዲያስፓራ አባላት አሁን ኢትዮጵያ ላላችሁ። የአሜሪካ ታክሳችሁን ካላችሁበት ሆናችሁ እንድታሰሩ ነገሮችን ሁሉ አስተካክለናል። ያልተሰራ የታክስ ውዝፍ (Back Tax)፣ መስተካከል ያለበት ታክስ (Amendment), የዚህ አመት ታክስ እና ሌሎችንም እንሰራለን።በViber ሆነ Whatspp ይደውሉልን። 619 255 5530 ። YebboTax info@yebbo.com Yebbo.com

Monday, January 10, 2022

"ኢትዮጵያዊነት ከዘር በላይ ነው" በሚል መሪ ቃል በሳንድያጎ ከተማ ለወገኖቻችን እርዳታ በተሰበሰብው ገንዘብ የእህል እርዳታ ይዞ የሄደው የልዑካን ቡድን ሰመራ ከተማ፣ አፋር ክልል ደረሰ።

"ኢትዮጵያዊነት ከዘር በላይ ነው" በሚል መሪ ቃል  በሳንድያጎ ከተማ ለወገኖቻችን እርዳታ  በተሰበሰብው ገንዘብ የእህል  እርዳታ ይዞ የሄደው  የልዑካን ቡድን  ሰመራ ከተማ አፋር ክልል ደረሰ።

የልኡካን ቡድኑ አባላት ወ/ሮ ቅድስት ብርሃኑ፣ አቶ አቶ ስዮም ደገፋ እና ወ/ሮ እመቤት እንግዳው 

(YebboMedia Jan 10,2022 ጥር ፪፣2ሺ፲፬) "ኢትዮጵያዊነት ከዘር በላይ ነው" በሚል መሪ ቃል  በሳንድያጎ ከተማ ለወገኖቻችን እርዳታ  እንዲደርስ ከተደረገው  የገንዘብ ማሰባሰቢያ ዝግጅት  ላይ ከተዋጣው $195000 ዶላር ላይ 60% የሚሆነው  በባንክ ቤት ቀጥታ ወደ ኢትዮጵያ በማስተላለፍ ኢትዮጵያ ሄዶ ከአገር ውስጥ የእርዳታ እህል  በመግዛት ወደ አፋር ክልል ያቀናው የልዑኳን ቡድን ሳመራ  ከተማ በመደረስ እርዳታውን ነገ  እንደሚያከፋፍል  ገለፀ። 40% የሚሆነው  በእርዳታ  የተሰበሰብ  ገንዘብ በ eyezonethiopia.com ላይ በተሰራው  የእርዳታ  ማሰሳበስቢያ ድረ ገፅ ላይ ገቢ መሆኑን  ባለፈው  ባጠናቀርነው ሪፖርት ላይ ተዘግቧል።  

የልዑካኑ  ቡድን  አስተባባሪ  የሆኑት  ወ/ሮ ቅድስት ብርሃኑ  በውስጥ  መስመር  እንደገለፁት  ዛሬ  ማምሻውን ሰመራ  ከተማ  የገቡ  ሲሆን  በነገው  እለት ለ800 አባወራዎች  የሚሆን 200 ኩንታል  የበቆሎ  ዱቄት፣ 80 ኩንታል ሩዝ፣ 2400 ሊትር ዘይት  የሚለግሱ ሲሆን ከዚህም  በተጨማሪ  ለ200 ቤተሰቦች 5 ፍይሎችን የሚያበረክቱ  መሆኑን  ገልፀውልናል።
  
በልዑካኑ ቡድን እቅድ መሰረት እረዳታውን በወሎ እና በአፋር ለተጎዱ ወገኖች ማከፋፈል ስለሆነ ሌላ  ተጨማሪ  መረጃ  ስናገኝ  ለንባብ  እናበቀዋለን።. 



                                            
ሪፖርተር፤ ዐም

No comments:

Post a Comment

Note: Only a member of this blog may post a comment.

Curated Products for Generation X

https://amzn.to/3VhbwJz GenX Essentials - Curated Products for Generation X ...

Do you need Ethiopian Power of Attorney where your agent can preform several crucial tasks on your behalf? Such as adoption proceedings, buying movable or immovable properties, paying tax, represent you in governmental and public offices and several others tasks with our your physical presence? If your answer is yes get the Ethiopian Power of Attorney or YEBBO now on sale

Shop Amazon