Saturday, November 21, 2020

Government will do everything possible to ensure stability in Tigray and free our citizens from harm and deprivation: Prime Minister Abiy Ahmed

መንግሥት በትግራይ ክልል መረጋጋት እንዲሰፍን እና ዜጎቻችን ከጉዳት እና እጦት ነፃ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ሁሉ ያደርጋል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ
****************************

የፌዴራል መንግሥት ለትግራይ ሕዝብ አጠቃላይ ደኅንነት እና ጤንነት ከፍተኛ ዋጋ የሚሰጥ ስለሆነ፣ በትግራይ ክልል መረጋጋት እንዲሰፍን እና ዜጎቻችን ከጉዳት እና እጦት ነፃ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርጉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ። 

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ሕግ ማስከበር ተልእኮው የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ባለፉት ጥቂት ቀናት ያስመዘገበው ድል የሚደነቅ ነው። 

ሠራዊታችን ትናንት ምሽት በአዲግራት ዙሪያ ያሉትን አካባቢዎች ከተቆጣጠረ በኋላ ዛሬ ደግሞ አዲግራትን ከሕወሓት ኃይል ሙሉ በሙሉ ነፃ አውጥቷል ብለዋል። 

የፌዴራል መንግሥት በተቆጣጠራቸው ከተማዎች እና አካባቢዎች የሚገኙ ዜጎች፣ በፀጥታ ኃይሎች ጥበቃ እየተደረገላቸው ወደ ዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸው መመለስ ጀምረዋል።
ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር በመሆን፣ ሰብአዊ እና ማኅበራዊ ፍላጎቶች የሚሟሉበትን መንገድ እናመቻቻለን ሲሉ ተናግረዋል። 

የሰብአዊ ድጋፍ ክንውኖችን ለመከታተል በፌዴራል መንግሥት የተዋቀረው ከፍተኛ ኮሚቴ፣ ተመጣጣኝ እና ወቅታዊ ድጋፍ ለማቅረብ የሚያስችል መረጃን እንዲያሰባስቡ ተጨባጭ ሁኔታውን የሚያጣሩ ልዑካንን ወደ ስፍራው መላኩንም ገልጸዋል።

በተጨማሪም ኮሚቴው ባለፉት ቀናት መኖሪያቸውን ጥለው የተሰደዱትን ዜጎች ሁሉ ወደ ቀዬአቸው ለመመለስ እና ለማቋቋም ከባለድርሻ አካላት ጋር መሥራቱን እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

Government will do everything possible to ensure stability in Tigray and free our citizens from harm and deprivation: Prime Minister Abiy Ahmed
 *******************************

 Prime Minister Abiy Ahmed said the federal government attaches great importance to the overall well-being and health of the people of Tigray.

 The success of the Ethiopian Defense Forces over the past few days is commendable.

 "Our forces took control of the area around Adigrat last night and today they have completely liberated Adigrat from the TPLF," he said.

 Citizens in federally controlled towns and areas began to return to normal activities under the protection of security forces.
 "We will work with the entire Ethiopian people to ensure that our humanitarian and social needs are met," he said.

 He said a high-level committee set up by the federal government to monitor humanitarian activities has sent a fact-finding mission to gather information to provide adequate and timely support.

 The committee also said it will continue to work with stakeholders to repatriate and resettle all displaced persons in the past few days.

No comments:

Post a Comment

Note: Only a member of this blog may post a comment.

የቦ ታክስ

ለዲያስፓራ አባላት በሙሉ እንዲሁም አሁን ኢትዮጵያ ላላችሁ። የአሜሪካ ታክሳችሁን ካላችሁበት ሆናችሁ እንድታሰሩ ነገሮችን ሁሉ አናስተካክላለናል። ያልተሰራ የታክስ ውዝፍ (Back Tax)፣ መስተካከል ያለበት ታክስ (Amendment) እንችላለን። የዚህ አመት ታክስ እና ሌሎችንም እንሰራለን።በViberም ሆነ Whatspp ይደውሉልን። ስልክ ቁጥራችን 619 255 5530 ነው ። YebboTax info@yebbo.com Yebbo.com

Translate

Do you need Ethiopian Power of Attorney where your agent can preform several crucial tasks on your behalf? Such as adoption proceedings, buying movable or immovable properties, paying tax, represent you in governmental and public offices and several others tasks with our your physical presence? If your answer is yes get the Ethiopian Power of Attorney or YEBBO now on sale

Shop Amazon

Call Yebbo

የቦ ኮሚኒኬሽን ኔት ወርክ ፣ ለ25 አመታት በላይ የስራ ልምድ ያካበተው የእናንተው በእናንተው። ከምሰጣቸው አገልግሎቶች ውስጥ የውክልና አገልግሎት መስጠት የኢትዮጵያ ፓስፖርት አገልግሎት መስጠት የቢጫ ካርድ የማውጣት አገልግሎት የታክስ አገልግሎት መስጠት (የትም የኢትዮጵያ ግዛት ይኑሩ) የጉዞ ወኪል የትርጉም ስራ አገልግሎት ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 619-255-5530 ይደውሉ።