Tuesday, December 1, 2020

ከሰሜን ዕዝ ከተለያዩ ብርጌዶችና ክፍለ ጦሮች ታግተው የነበሩ 1240 የመከላከያ ሰራዊት አባላት ወደ ሠቆጣ ገቡ

ከሰሜን ዕዝ ከተለያዩ ብርጌዶችና ክፍለ ጦሮች ታግተው የነበሩ 1240 የመከላከያ ሰራዊት አባላት ወደ ሠቆጣ ገቡ
*****************************
ከሰሜን ዕዝ ከተለያዩ ብርጌዶችና ክፍለ ጦሮች በጁንታው ኃይል ታግተው የነበሩ 1240 የመከላከያ ሰራዊት አባላት ወደ ዋግኸምራ ዞን ሰቆጣ ሠቆጣ ከተማ ገብተዋል።

የሠራዊት አባላቱ ከህዳር 20፣2013 ዓ.ም ከ 8 ሰዓት ጀምሮ እስከ እስከ ትላንት ማታ 12 ሰዓት ድረስ ነው ወደ  ሰቆጣ የገቡት። 

የመከላከያ ሰራዊት አባላቱ ሰቆጣ ለመግባት በርካታ ውጣ ውረድ  ማለፋቸውንም ገልጸዋል።
በተለይም የተከዜን ኮሪደር ተከትለው በቀን እና  ሌሊት የእግር ጉዞ  እንዲሁም ወንዝና ጫካ እያቆራረጡ ሰቆጣ  መግባታቸውን የሠራዊቱ አባላት ተናግረዋል።

የአካባቢው  አስተዳደር ለሰራዊቱ የምግብ እና የህክምና አቅርቦት ማመቻቸቱም ተመልክቷል።
 
በራሄል ፍሬው

No comments:

Post a Comment