የቦ ታክስ

ለዲያስፓራ አባላት አሁን ኢትዮጵያ ላላችሁ። የአሜሪካ ታክሳችሁን ካላችሁበት ሆናችሁ እንድታሰሩ ነገሮችን ሁሉ አስተካክለናል። ያልተሰራ የታክስ ውዝፍ (Back Tax)፣ መስተካከል ያለበት ታክስ (Amendment), የዚህ አመት ታክስ እና ሌሎችንም እንሰራለን።በViber ሆነ Whatspp ይደውሉልን። 619 255 5530 ። YebboTax info@yebbo.com Yebbo.com

Monday, November 16, 2020

የዩጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ በኢትዮጵያ ድርድር እንዲደረግ የጠየቁበትን የትዊተር መልዕክት አጠፉ

የዩጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ በኢትዮጵያ ድርድር እንዲደረግ የጠየቁበትን የትዊተር መልዕክት አጠፉ። ፕሬዝዳንቱ ከምክትል ጠቅላይ ምኒስትር ደመቀ መኮንን ከተነጋገሩ በኋላ "ጦርነት በኢትዮጵያ ለአጠቃላይ አኅጉሩ የከፋ ምስል ይሰጣል። ድርድር ተደርጎ ግጭቱ ሊቆም ይገባል። አለበለዚያ ወደ አላስፈላጊ የሰው ሕይወት መጥፋት ይመራል። ኤኮኖሚውንም ያሰናክላል" ብለው ነበር። 
ሙሴቬኒ ከምክትል ጠቅላይ ምኒስትር ደመቀ መኮንን አብረው ሲጓዙ እና ሲነጋገሩ የሚያሳዩ ምስሎች እና ፕሬዝዳንቱ የጻፏቸው መልዕክቶች አሁንም በይፋዊ የትዊተር ገፃቸው ቢገኙም "ድርድር ሊደረግ ይገባል" የሚል መልዕክት ያዘለው ግን ተለይቶ ጠፍቷል።

ዛሬ በአዲስ አበባ ፒያሳ ደጎል አደባባይ የተፈጠረው ምንድን ነው?

ህዳር 7፣2013

ዛሬ በአዲስ አበባ ፒያሳ ደጎል አደባባይ  የተፈጠረው ምንድን ነው? 

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን መግለጫ ሙሉ ቃል የሚከተለው ነው፦

በአራዳ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ደጎል አደባባይ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ  ፖሊስ ፈንጂ አመከነ በሚል በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የተለቀቀው መረጃ ሐሰተኛ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አሰታወቀ፡፡

ዛሬ ህዳር 7፣2013 ዓ.ም በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ፒያሳ ደጎል አደባባይ አካባቢ ከሰዓት በፊት በጎዳና ላይ ተዳዳሪ የሆነ አንድ ግለሰብ በማዕድን ውኃ መያዣ ላስቲክ ድራፍት በመግዛት ለመጠጣት ወደ አንድ ጥግ መሄዱ ያጠራጠራቸው በአካባቢው በጫማ መስዋብ ሥራ ላይ ተሰማሩ ወጣቶች ለፖሊስ ባደረሱት ጥቆማ የአካባቢው ፖሊስ እና የፌዴራል ፖሊስ ፈንጂ አምካኝ ባለሙያዎች ቦታው ላይ በመገኘት ተከሰተ የተባለውን  ማረጋገጥ መቻላቸውን ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡

ካለው ወቅታዊ ሁኔታ አንፃር አካባቢያቸውን በንቃት የሚጠብቁ ወጣቶች መበራከታቸው የሚደነቅ ቢሆንም ለፖሊስ የሠጡትን መረጃ በመንተራስ ፖሊስ ባረጋገጠው መሰረት በላስቲክ የተሞላ ድራፍት ቢራ እንጂ ፈንጂ አለመሆኑን ህብረተሰቡ እዲገነዘብ ኮሚሽኑ አሳስቦ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች በሚለቀቁ  ሐሰተኛ መረጃዎች እንዳይደናገጥ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን መልዕክቱን ያስተላልፋል፡፡


The campaign against Wayane Junta is a national goal of upholding the rule of law," said Gedu Andargachew, the prime minister's national security adviser.




"በህውሓት ጁንታ ላይ የሚካሄደው ዘመቻ የህግ የበላይነትን በማስከበር አገራዊ ግብ ያነገበ ነው" የጠቅላይ ሚኒስትሩ ብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር  ገዱ አንዳርጋቸው 
*********************

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር  ዐብይ አህመድ የተላከ መልዕክት ለጂቡቲው ፕሬዚደንት ኢስማኤል ዑመር ጊሌ  አድርሰዋል፡፡

አቶ ገዱ አንዳርጋቸው  ከጅቡቲው ፕሬዘዳንት ጋር በነበራቸው ቆይታ  በህውሓት ጁንታ ላይ የሚካሄደው ዘመቻ የህግ የበላይነትን በማስከበር፣ ወንጀለኞችን ለፍርድ የማቅረብና ህገ መንግስታዊ ስርዓትን የማስጠበቅ አገራዊ ግብ ያነገበ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የጂቡቲው ፕሬዚደንት ኢስማኤል ዑመር ጊሌ ከአገራቸው ጋር በደም፣ በቋንቋና በባህል ብሎም በምጣኔ ሃብት ለተሳሰረችው ኢትዮጵያ ሰላምና አንድነት ያላቸውን ሙሉ ድጋፍ ገልጸዋል፡፡ 

 ፕሬዚደንቱ የጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ መንግስት ቁልፍና በጎ ሚና የአገሪቱን ሰላም፣ አንድነትና እድገት የሚያስጠብቅ ነው ብለዋል።

"The campaign against Wayane Junta is a national goal of upholding the rule of law," said Gedu Andargachew, the prime minister's national security adviser.
 *********************

 The Prime Minister of the Federal Democratic Republic of Ethiopia, Gedu Andargachew, conveyed a message from Prime Minister Abi Ahmed to the President of Djibouti, Ismail Omar Guelleh.

 During his meeting with the President of Djibouti, Gedu Andargachew said the campaign against the TPLF is aimed at upholding the rule of law, bringing criminals to justice and upholding the constitutional order.

 Djibouti's President Ismail Omar Guelleh has expressed his full support for peace and unity in Ethiopia, which is bound by blood, language, culture and economy.

 He said the key role of the government of Prime Minister Abi Ahmed is to safeguard the country's peace, unity and development.

በትግራይ ክልል መቀሌ ሀራ ገበያ ዓዲ ጉደም ምድር ባቡር ፕሮጀክት በሚጠብቁት ላይ ከተፈጸመ ጥቃት የተረፉት ሁለት የፌደራል ፖሊስ አባላት አዲስ አበባ ከተማ ገብተዋል፡፡

በትግራይ ክልል መቀሌ ሀራ ገበያ ዓዲ ጉደም ምድር ባቡር ፕሮጀክት በሚጠብቁት ላይ ከተፈጸመ ጥቃት የተረፉት ሁለት የፌደራል ፖሊስ አባላት አዲስ አበባ ከተማ ገብተዋል፡፡
***********************************************
አዲስ አበባ፣ህዳር፣07-2013 ዓ.ም

የህዝብና መንግስት መሰረተ ልማቶችን በመጠበቅ ከ10 ዓመታት በላይ መቆየታቸውን የገለጸው ዋና ሳጅን ድረስ ስንሻው የተለመደዉን መደበኛ የጥበቃ ስራችን እያከናወን በነበርንበት ወቅት በፕሮጀክቱ ባሉ ሳይቶች ላይ የነበሩ የስራ ባልደረቦቻችንን ትጥቅ በማስፈታት፣ አፍነውና እጃቸውን በካቴና አስረው ወደ መቀለ ሲወስዷቸው እጃችንን ከምንሰጥ ብለን ወደ ጫካ በመግባት ለሚተኮስብን ተኩስ ምላሽ በመስጠት ለማምለጥ ችለናል ብለዋል፡፡

እኛ ለአንድ ብሔር የቆምን ሳይሆን ከሁሉም ብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የተውጣጣንና ሀገራችን ኢትዮጵያ በአንድነት ስንጠብቅ የኖርን በመሆኑ እንደዚህ አይነት የሀገር ክህደት ይፈጸምብናል ብለን አልጠበቅንም ነበር በማለት ገልጸዋል፡፡

የታፈኑ አባሎቻችንን ለማስለቀቅ ብንሞክርም ከአቅማችን በላይ በመሆናቸውና እኛንም ለማስቀረት ከፍተኛ የሆነ ቶክስ ስለ ከፈቱብን ለጽንፈኛው ቡደኑ እጅ ከምንሰጥ በማለት ለሶስት ቀናት የሚበላና የሚጠጣ ባልነበረበት በበረሃ ጫካ ለጫካ እየተጓዘን አፋር ክልል ስንደርስ አባላ የሚባል አካባቢ የክልሉ ህዝብ ተቀብሎን ወደ መስመር አወጣን ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የህወሓት ጽንፈኛ ቡድኑ በእኛ በፌደራል ፖሊስ አባላትና በሀገር መከላከያ ሰራዊት የፈጸመው አረመናዊ ድርጊት በጣም አሳዝኖናል፣በተለይ ከ10 ዓመታት በላይ አብሮን የሰሩና የኖሩ የትግራይ ተወላጅ የፖሊስ አባላት ወደ ክልሉ ልዩ ሀይል በመቀላቀል አፈሙዝ ወደ እኛ በማዞር የፈጸሙብን ክህደት በጣም አሳዝኖናል፣ አስከፍቶናልም ብለዋል፡፡
 
ከዚህ ቀደም አባት አርበኞች ከፍተኛ መስዋትነት ከፍለው ኢትዮጵያን እንዳስረከቡን ሁሉ ዛሬም በርካታ የሀገር ተቆርቃሪ የሆኑ ጓዶች ስላሉን ሀገራችን ለማዳን እየተከናወኑ ያሉ የህግ ማስከበር ስራዎች ስኬታማ እንዲሆኑ እስከ መጨረሻ ከህዝብ ጋር በመቆም ለዚህ አስነዋሪ ድርጊት የተሰለፉትን የህወሓት ፅንፈኛ ቡድን ለህግ ለማቅረብ ለሚደረገው ርብርብ ኃላፍነታቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡

 ሌላኛዉ የሰሜን ዲቪዥን፣ሶስት፣ሻለቃ 4፣ሻምበል 1 አባል ኮንስታብል ድረስ ንጉሴ እኛ ሰላም ነው ብለን በተቀመጥንበትና ባላሰብነው ሰዓት የክልሉ ልዩ ሃይልና ሚሊሻ ተደራጅተው በመምጣት አንድ ዳቦ ለሁለት በመካፈል አብረውን ሲበሉ ከነበሩ ከትግራይ ተወላጅ የስራ ባልደረቦቻችን ጋር በመሆን ጥቃት ቢፈጽሙብንም የአፋር ህዝብ ላደረገልን አቀባበልና ድጋፍ ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል፡፡

እኛ የትግራይ ህዝብን ከወንጀል በመከላከልና በክልሉ የሚገኙ መሰረተ ልማቶችን በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ማህበራዊ እንቅስቃሴ ስናግዝና ስንተባበር ነው የቆየነው፣የትግራይ ህዝብ ይህንን ጽንፈኛ ቡድን በማጋለጥ ነጻነቱን ሊያረጋግጥ ይገባልም ብሏል፡፡

ጀግናው አየር ሃይል ስለደመሰሰው ሚሳይል

መረጃ
ጀግናው አየር ሃይል ስለደመሰሰው ሚሳይል
[ S-125 SA-3 GOA ]
ትህነግ ለሽብር ጥቃት ያዘጋጀችው ሚሳይል ሲስተም ትናንት በአየር ሃይላችን መደምሰሱ ይታወሳል። የእስራኤል ወታደራዊ ዌብሳይትም ሳይቱን ይፋ አድርጓል። ጥቂት ስለ ሚሳይሉ...
ራሺያ ሰራሽ ነው። በመካከለኛ የከፍታ ወለል ላይ ከምድር ወደ አየር የሚተኮስ ሚሳይል ሲስተም፤ Accuracy ው 650 ሜትር፤ እንደ ሲስተሙ ሁኔታ ከ 200 ኪ.ሜ በላይ ይጓዛል።
S-125 ሚሳይል ለተኩስ ሲዘጋጅ እስከ 90 ° የሚሽከረከር አራት ማዕዘን ቦርድ ዝግጅቱን ያስጀምራል። አራት የ 2.6 ሰከንድ የዝግጅት ማቀጣጠያ ቆይታ ያላቸው ክፍሎች ያሉት። ለጉዞ ማራዘሚያ ዘላቂ ሞተር የተገጠመለት፤ አራት አራት ቀጥ ያሉ ክንፎችና አራት ወደፊት ተንቀሳቃሽ መቆጣጠሪያ አለው ፡፡ ሚሳኤሉ ከበስተኋላ ክንፎቹ ላይ ወደ አንቴናው ከሚላከው guiding ምልክቶች የሲስተም ራዳር ክትትል ይደረግበለል፡፡ 2 የተለያዩ ሚሳይሎችን ይጠቀማል።
S-125 ከፊል ተንቀሳቃሽ ነው፣ ሚሳኤሎቹ በሁለት ወይም አራት ቋሚዎች ይተከላሉ። በ ZIL መኪናዎች ላይ ሲሆን ጥንድ ጥንድ ሆነው ለተልዕኮ ሊዘጋጁ ይችላሉ ፡፡
የታጠቁት አገራት
ኢትዮጵያ [የተወሰነው በጁንታው ዕጅ] ፣ሰሜን ኮሪያ፣ ሩሲያ፣ ግብፅ፣ ሕንድ፣ አዘርባጃን፣ አልጄሪያ፣ አንጎላ፣ አርሜኒያ፣ ቡልጋሪያ፣ በርማ፣ ካምቦዲያ፣ ቼክ ሪፐብሊክ፣ ኩባ፣ ፊንላንድ፣ ፖላንድ፣ ሶማሊያ፣ ዩክሬን፣ ታንዛኒያ፣ ቬትናም እና ሌሎችም ይገኛሉ።

በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የተመራ የልዑካን ቡድን ናይሮቢ ገባ።





በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የተመራ የልዑካን ቡድን ናይሮቢ ገባ።

ህግ የማስከበሩ ዘመቻ የውስጥ ጉዳያችንን በራሳችን አቅም መልክ ለማስያዝ የሚካሄድ በመሆኑና "አክራሪው ሃይል" በህግ ስር ከመሆኑ በፊት ምንም አይነት የውጭ ሃይል እንቅስቃሴ ስርዓት አልበኝነትን በማንገስ የሀገራችንን ሰላም የማደፍረስ ውጤት የሚያስከትል መሆኑን መንግስት አቋሙን ግልፅ አድርጓል።

ይህንኑ አቋም በማስረዳት የቀጠናው አገራት መንግስት የጀመረውን ህግና ህገ መንግስት የማጽናት ጥረት እንዲደግፉ ለማስቻል የጠቅላይ ሚኒስትሩን መልዕክት የያዘና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የተመራ የልዑካን ቡድን ከኬንያው ፕሬዝደንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል።

ምንጭ: በናይሮቢ የኢትዮጵያ ኤምባሲ

#Ethiopia #Ethiopian #kenya

"የህግ ማስከበር ዘመቻው በጽንፈኛው የሕወሓት ጁንታ ላይ ብቻ ያተኮረ ነው"፡- የአገር መከላከያ ሠራዊት አባላት

"የህግ ማስከበር ዘመቻው በጽንፈኛው የሕወሓት ጁንታ ላይ ብቻ ያተኮረ ነው"፡- የአገር መከላከያ ሠራዊት አባላት
*****************

የእተከናወነ ያለው የህግ ማስከበር ዘመቻ በጽንፈኛው የሕወሓት ጁንታ ላይ ብቻ ያተኮረ እንደሆነ በዘመቻው ላይ እየተሳተፉ ያሉ የአገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ተናገሩ።

ጽንፈኛው የሕወሓት ጁንታ ባለፉት ሁለት ዓመታት የተለያዩ ህገ ወጥ ድርጊቶችን በማቀነባበርና የፋይናንስ ድጋፍ በማድረግ ለበርካታ ዜጎች ህይወት መቀጠፍና መፈናቀል እጁ እንዳለበት በተደጋጋሚ ሲጠቀስ ቆይቷል።

መንግስት በትግራይ ክልል የመሸገውን ፅንፈኛ የሕወሓት ጁንታ ለሕግ ለማቅረብ እየወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ኢዜአ ያነጋገራቸው የአገር መከላከያ ሰራዊት አባላት እንደሚሉት፤ ሰራዊቱ ጽንፈኛ ቡድኑን ለህግ ከማቅረብ ባለፈ ማናቸውንም አይነት የውስጥና የውጭ ጥቃት የመመከት ቁመና ላይ ይገኛል።

ይህን አቅሙን በመጠቀምም በትግራይ ክልል የመሸገውን የሕወሓት ጁንታ ለህግ ለማቅረብ የህግ ማስከበር ተግባር እየተከናወነ መሆኑንም ነው ያስረዱት።

ህግ ማስከበሩ ስራ በትግራይ ስም በመሸገው ህገ ወጥ ቡድን ላይ ብቻ ያተኮረ እንጂ በቡድኑ ጭቆና ስር የነበረውን የትግራይ ህዝብ እንደማይመለከት ነው የሚናገሩት።

ከዚህ አንጻር መከላከያ ሰራዊቱ ከወገኑ የትግራይ ህዝብ ጋር ያለው አብሮነት ተጠናክሮ የሚቀጥል ስለመሆኑ አረጋግጠዋል።

የህግ ማስከበሩ ስራ የትግራይን ህዝብ ከጭቆና እና አፈና ነጻ የሚያወጣ በመሆኑ የክልሉ ነዋሪ ከመከላከያ ጎን በመሆን እያከናወነ ያለውን ድጋፍና እገዛ እንዲያጠናክር ጥሪ አቀርበዋል።


Curated Products for Generation X

https://amzn.to/3VhbwJz GenX Essentials - Curated Products for Generation X ...

Do you need Ethiopian Power of Attorney where your agent can preform several crucial tasks on your behalf? Such as adoption proceedings, buying movable or immovable properties, paying tax, represent you in governmental and public offices and several others tasks with our your physical presence? If your answer is yes get the Ethiopian Power of Attorney or YEBBO now on sale

Shop Amazon