Shop Amazon

Tuesday, October 30, 2018

በምዕራብ ወለጋና በቄለም ወለጋ የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ አካላት እጃቸውን መሰብሰብ አለባቸው:- አቶ ለማ መገርሳ

በምዕራብ ወለጋና በቄለም ወለጋ የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ አካላት እጃቸውን መሰብሰብ አለባቸው:- አቶ ለማ መገርሳ
********************************

በምዕራብ ወለጋና ቄለም ወለጋ ዞኖች በኦነግ ስም ታጥቆ የሚንቀሳቀስና ህዝቡን ለችግር እየዳረገ ያለው አካል እጁን መሰብሰብ አለበት ብለዋል የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ለማ መገርሳ፡፡

ፕሬዝዳንቱ መንግስት ይህንን ድርጊት በትዕግስት ሲከታተል መቆየቱን  ገልጸው፣ ከዚህ በኋላ የህዝቡ ደህንነት እንዲጠበቅና ሕግ እንዲከበር እንሰራለን ብለዋል፡፡

ህዝቡም ሆነ የአገር ሽማግሌዎች በዚህ ድርጊት  የተሳተፉ አካላት ከድርጊታቸው ተቆጥበው ወደ ሰላማዊ መንገድ እንዲመለሱ ጥሪ እንዲያቀርቡላቸው ጠይቀዋል አቶ ለማ መገርሳ፡፡

ምንጭ: OBN

Monday, October 29, 2018

ፈረንሳይ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ለመታደግ በሚደረገው ጥረት ድጋፍ እንደምታደርግ ገለፀች

ፈረንሳይ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ለመታደግ በሚደረገው ጥረት ድጋፍ እንደምታደርግ ገለፀች
*************************************************************************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከፈረንሳዩ ፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር በፖለቲካዊና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ዙሪያ በፓሪስ መክረዋል፡፡

ሀገራቱ የቆየ ወደጅነታቸውን በማጠናከር ለተሻለ ለውጥ እንደሚሰሩም ተናግረዋል፡፡

ሰላምና ደህንነት፣ንግድና ኢንቨስትመንት ፣ ትምህርትና ባህል ደግሞ በጋራ ለመስራት ከተስማሙባቸው ዘርፎች ይጠቀሳሉ᎓፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድና ፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ከሁለትዮሽ ውይይታቸው በኋላ በሰጡት መግለጫ  እንዳስታወቁት የሀገራቱን ትብብር የበለጠ ለማሳለጥ ይሰራል፡፡

ፈረንሳይ በቅርስ ጥበቃ ያላትን አቅም የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ለመታደግ እንድታውለው የቀረበላትን ጥሪ እንደተቀበለች ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ገለፀዋል፡፡

በአፍሪካ ቀንድ በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል የመጣውን ሰላም በማስቀጠል በኤርትራና በጅቡቲ መካከል ሰላም እንዲጠናከር ለማድረግ በጋራ ለመስራት ከስምምነት መደረሱንም አስታውቀዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ አማካኝነት በኢትዮጵያ እየመጣ ያለውን ለውጥ ለመደገፍ ሀገራቸው ዠግጁ እንደሆነች ገልፀዋል፡፡

በቴሌኮም በትራንስፖርት በመሰረተልማት ዘርፍ የመሳተፍ ፍላጎት  እንዳላትም እንዲሁ፡፡

ከቀጠናው ሰላም ጋር በተያያዘ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እያደረጉ ያሉትን ተግባር እንደግፋለን እናደንቃለንም፤በተለይ በሳቸው ተነሳሽነት በኢትዮጵያና በኤርትራ የተፈጠረውን ሰላም በተመለከተ ልዩ አክብሮት አለን ፤ቀሪው የሰላም ሂደት የተሳካ እንዲሆንም ድጋፍ እናደርጋለን ፤ከኤርትራ ከጅቡቲም ሆነ ከሌሎች የቀጠናው ሀገራት ጋር ኢትዮጵያ እየፈጠረች ያለቸውን የሰላምና የትብብር መንፈስ እንደፈረንሳይ ብቻ ሳይሆን እንደ አውሮፓ ህብረት የምንደግፈው ነው ብለዋል ፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን፡፡

ከሁለት ወራት በኋላም የተጀመረውን ግንኙነት ለማጠናከር ወደ ኢትዮጵያ እነደሚመጡም ተነግረዋል፡፡
በብሩክ ያሬድ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፈረንሳይ ፓሪስ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፈረንሳይ ፓሪስ ገቡ
************************
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ለስራ ጉብኝት ፈረንሳይ ፓሪስ ገብተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፈረንሳይ ቆይታቸው ከፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ዶ/ር ዐቢይ ከፈረንሳይ ጉብኝት በኋላ ወደ ጀርመን ያቀናሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ሪፖርተራችን ብሩክ ያሬድ ከፓሪስ ዘግቧል፡፡

ፎቶ:- አቶ ፍጹም አረጋ፣ ብሩክ ያሬድ

ኮ/ል ጎሹ ወልዴ አዲስ አበባ ገቡ

ኮ/ል ጎሹ ወልዴ አዲስ አበባ ገቡ
**********************************
በደርግ ዘመነ መንግስት የአገራችን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና የትምርት ሚኒስትር የነበሩት ኮ/ል ጎሹ ወልዴ ዛሬ አዲሰ አበባ የገቡ ሲሆን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሂሩት ዘመነና እና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአሜሪካ ጉዳዮች ዳ/ጀነራል አቶ ነብያት ጌታቸውን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች አቀባበል አድርግውላቸዋል።

የቀድሞው ሚኒስትር በቦሌ ዓለምአቀፍ አየር መንገድ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የደርግን አገዛዝ በመቃወም ሃላፊነታቸውን በፈቃዳቸው ከለቀቁና ኑሯቸውን በአሜሪካ ካደረጉ ጀምሮ ላለፉት 32 አመታት የአገራቸውን መሬት ሲረግጡ የመጀመሪያቸው መሆኑን ገልጸው አመጣጣቸው የአገራችንን አጠቃላይ የለውጥ ሂደት ለማየት፣ ለረጅም ጊዜ የናፈቋቸውን ዘመድ ወዳጆች ለማግኘትና የተጀመረውን የሰላም፣ የፍቅርና የመደመር ሂደት በሚችሉት መጠን ለመደገፍ መሆኑን ገልጸዋል።

ምንም አይነት ፖለቲካዊ ውድድር የማድረግም ሆነ ስልጣን የማግኘት ፍላጎት የለኝም ያሉት ኮ/ል ጎሹ በአሁኑ ወቅት በአገራችን የተጀመረው የሰላም፣ የእርቅና የመደመር እንቅሴቃሴ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ በመሆኑ እርሳቸውን ጨምሮ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊደግፈው እንደሚገባ በማመን መምጣታቸውን ጠቁመው ለዚህም ለኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ወጣቱ የሰላምን አስፈላጊነት በሚገባ ተገንዝቦ ለግጭት ከሚዳርጉ እንቅስቃሴዎች እንዲቆጠብ ጥሪ አቅርበው ማንኛውንም ጥያቄዎች በሰላማዊ መንገድ በማቅረብ መፍትሄ ማግኘት የሚያስችል ሁኔታ ተፈጥሯል የሚል እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል።

ለዚህም ያላቸውን ልምድና ተሞክሮ ለማጋራትና ለሰላማዊ ሂደቱ መጎልበት የተቻላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት ቃል ገብተዋል።

ምንጭ፡- የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

Sunday, October 28, 2018

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የመጀመርያ የአውሮፓ ጉብኝታቸውን በፈረንሳይ ለመጀመር ነገ ወደ ፓሪስ ያቀናሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የመጀመርያ የአውሮፓ ጉብኝታቸውን በፈረንሳይ ለመጀመር ነገ ወደ ፓሪስ ያቀናሉ።
*******************************************************************ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፈረንሳይ ቆይታቸው ከፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር የሁለቱን ሀገራት የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ይመክራሉ።

የፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ በኢትዮጵያ ተሳትፎውን እንዲያሳድግ እንዲሁም በፈረንሳይ ያለውን ቅርስን የመጠበቅና የመንከባከብ ክህሎት የኢትዮጵያ ቅርሶችን ለመታደግ መዋል በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ይወያያሉ።

ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ወደ ፈረንሳይ ያቀኑት ኢማኑኤል ማክሮን ከወራት በፊት ያቀረቡላቸውን ግብዣ ተከትሎ ነው።

ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ ከፓሪስ ቆይታ በኋለ ወደ ጀርመን በርሊን በማቅናት  የቡድን 20 አባል ሀገራት በሚያዘጋጁትና በአፍሪካ ጉዳይ ላይ በሚመክረው ኮምፓክት አፍሪካ ጉበኤ ላይ ይሳተፋሉ።

በጀርመን አነሳሽነት የተቋቋመው ይህ የአፍሪካ የልማት ድጋፍ መርሐግብር ኢትዮጵያን ጨምሮ ሰባት የአፍሪካ ሀገራትን ማዕከል ያደረገ ነው።

ጠቅላይ ሚንስትሩ በጀርመን ቆይታቸው ከመራሂተ መንግስት አንጌላ ሜርክል ጋር ተገናኝተው የሁለቱን ሀገራት የልማት ትብብር የበለጠ ለማጠናካር በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ይወየያሉ።

ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ከ2018 እስከ 2020 የሚቆይ የ213 ሚሊዮን ዩሮ የልማት ትብብር በቅርቡ መፈራረሟ ይታወሳል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ፍራንክ ፈርት በማምራትም አንድ ሆነን አንነሳ ነገን እንገባ በሚል መርህ በተዘጋጀው የኢትዮጵያውያን መድረክ ላይም ይገኛሉ።

በዚህ መድረክ ከ20ሺ በላይ ከመላው አውሮፓ የተውጣጡ ኢትየጵያውያን ከጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ጋር ይወያያሉ በሀገራቸው ሁለንተናዊ ልማት ላይ በሚሳተፉበት መንገድ ላይም ይመክራሉ  ።

በብሩክ ያሬድ

Thursday, October 18, 2018

Ethiopia's Prime Minister Abiy Ahmed has said that some of the soldiers who entered the grounds of his office last week had wanted to kill him.

Ethiopia's Prime Minister Abiy Ahmed has said that some of the soldiers who entered the grounds of his office last week had wanted to kill him.

At the time, he defused the situation by ordering them to do press-ups and joining in.

Mr Abiy and the soldiers were seen laughing but he told parliament that "inside I was very unhappy".