የቦ ታክስ
ለዲያስፓራ አባላት አሁን ኢትዮጵያ ላላችሁ። የአሜሪካ ታክሳችሁን ካላችሁበት ሆናችሁ እንድታሰሩ ነገሮችን ሁሉ አስተካክለናል። ያልተሰራ የታክስ ውዝፍ (Back Tax)፣ መስተካከል ያለበት ታክስ (Amendment), የዚህ አመት ታክስ እና ሌሎችንም እንሰራለን።በViber ሆነ Whatspp ይደውሉልን። 619 255 5530 ። YebboTax info@yebbo.com Yebbo.com
Wednesday, January 5, 2022
Journalist Hermela arrives in Addis Ababa
ጋዜጠኛ ሄርሜላ አረጋዊ አዲስ አበባ ገባች
የሽብር ቡድኑን ትሕነግና የአጋሮቹን ወንጀል ለዓለም በማጋለጥና በመሟገት የምትታወቀው ጋዜጠኛ ሄርሜላ አረጋዊ ዛሬ ጠዋት አዲስ አበባ ገባች።
ጋዜጠኛዋ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም ዐቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ስትደርስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ አቀባበል አድርገውላታል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ለ1 ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እንዲሁም የኢትዮጵያ ወዳጅ ዲያስፖራዎች ያቀረበውን የወደ አገር ቤት ግቡ ጥሪ ተከትሎ ነው ጋዜጠኛ ሄርሜላ አዲስአበባ የገባችው።
የሲቢኤስ ጋዜጠኛና ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ሄርሜላ ከኢትዮጵያ አጀንዳነት ተሻግሮ ዓለም ዐቀፍ ንቅናቄ የሆነውን እምቢ ለባርነት ወይም የበቃ #Nomore እንቅስቃሴን በማስጀመርም ትታወቃለች።
Journalist Hermela arrives in Addis Ababa
Hermela Aregawi, a journalist known for exposing and defending the terrorist group and its affiliates, arrived in Addis Ababa this morning.
Upon arrival at Addis Ababa Bole International Airport, the journalist was welcomed by senior officials of the Ministry of Foreign Affairs and Athlete Major Haile Gebreselassie.
Hermela arrived in Addis Ababa following a call by the Ethiopian government for a homecoming of 1 million Ethiopians, Ethiopians of Ethiopian descent and friends of the Ethiopian Diaspora.
Hermesla, a CBS journalist and Ethiopian-born, is also known for launching the #Nomore movement, an international movement that has gone beyond the Ethiopian agenda.
(Pole)
(ዋልታ)
በአዲስ አበባ የድህረ ጦርነት ዝንፈቶችን ፈጥኖ ማረም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሲከናወን የነበረው የውይይት መድረክ ተጠናቀቀ
በአዲስ አበባ የድህረ ጦርነት ዝንፈቶችን ፈጥኖ ማረም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሲከናወን የነበረው የውይይት መድረክ ተጠናቀቀ
****************************
የድህረ ጦርነት ዝንፈቶችን ፈጥኖ በማረም ሁለንተናዊ ድል እስከሚረጋግጥ በጦርነቱ ውስጥ የተገኙ ትሩፋቶችን አጠናክረን ድላችንን የመጠበቅና የማስፋት ዓላማ የያዘው የውይይት መድረክ የአጠቃላይ ክፍለ ከተማና የወረዳ አመራር ውይይት ማጠቃለያ በፕላዝማ ተካሂዷል::
በክፍለ ከተማ እና በወረዳ ባሉ አጠቃላይ አመራር ባለፉት ሶስት ቀናት የኢትዮጵያን ህልውና ለማስጠበቅ ሲባል በተካሄደው ትግል የተገኙ አንጸባራቂ ድሎችን ማስጠበቅ በሚቻልበት ሁኔታ እና የድህረ ጦርነት ዝንፈቶችን ፈጥኖ ማረም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ሲያደርጉ ቆይተዋል።
በውይይቱ ወቅትም ኢትዮጵያ ተገዳ የገባችበትን ጦርነት በውድ ልጆቿ መስዋዕትነት ድል ያስመዘገበች በመሆኑ ይህ የተገኘውን ድል መጠበቅና ማስፋት እንደሚገባ ተገልጿል።
የማጠቃለያ ውይይቱን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣ የአዲስ አበባ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ ቤት ሃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ እና የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባና የስራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ መምራታቸውን ከከተማ አስተዳደሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
New year, new location for Yebbo.com
After serving our customers for more than 20 years in one location finally we are moved to a new location. We are not that very far away from our old location. The new address is located at the historic El Cajon Blvd . Our new address is 3078 El Cajon Blvd. San Diego, CA 92104.
This year we are more that ready to serve our tax clients. This year tax will be much different and unique , most of our clients will have unemployment payment, grant, SBA Loan, PPP loan and all sort of incomes. We are ready to tackle all unique incomes.
ማሳሰቢያ! እናት ኢትዮጵያ ያደረገችውን ጥሪ ተቀብላችሁ በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ለምትገኙ የአሜሪካ ነዋሪዎች የዚህን አመት የታክስ መሙላት ጊዜ ያልፍብናል ብላችሁ የሄዳችሁበትን አላማ ሳታሳኩ በቶሎ እንዳትመለሱ። ይህንን ችግር አሳቤ ውስጥ በማስገባት የቦታክስ እናንተ እዚያው ኢትዮጵያ ሆናችሁ ታክሳችሁን ማሰራት እንደምትችሉ ሁኔታወችን ሁሉ ያመቻቸን መሆኑን ስንገልፅ በታላቅ ደስታ ነው። በበለጠ ለመረዳት በviber or Whatsapp ደውላችሁ እንዴት ማድረግ እንዳለባችሁ መጠየቅ ትችላልሁ።
እኛ የትም አገር ይኑሩ የአሜሪካን ታክስ መሙላት እንችላለን፣
በነዚህ መነገዶች እኛን ማግኘት ትችላላችሁ ።
Phone : 619 255 5530
email: info@yebbo.com
Fax: 6192829326
Web Site: www.yebbo.com
Facebook: http://www.facebook.com/yebbo
Huawei Technology Group Supports Ethiopia's International Internet Governance Conference -
ኢትዮጵያ የምታዘጋጀውን ዓለም አቀፍ የኢንተርኔት አስተዳደር ጉባኤን እደግፋለሁ - ሁዋዌ ቴክኖሎጂ ግሩፕ
**********************
ሁዋዌ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ኢትዮጵያ በቀጣይ ዓመት የምታዘጋጀውን ዓለም አቀፍ የኢንተርኔት አስተዳደር ጉባኤን በገንዘብ እና በቴክኒክ እንደሚደግፍ አስታወቀ።
የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ ከሁዋዌ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ምክትል ሥራ አስፈፃሚ ቻርለስ ዲንግ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።
ድርጅቱ በኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍም ከመንግሥት እና ከግሉ ዘርፍ ጋር በጋራ መሥራት እንደሚፈልግ ምክትል ሥራ አስፈፃሚው ጠቁመዋል።
የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ ሁዋዌ ዓለም አቀፍ የኢንተርኔት አስተዳደር ጉባኤ ዝግጅትን ለመደገፍ ቃል በመግባቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ሁዋዌ የቴክኖሎጂ ግሩፕ በዓለም ላይ ካሉት ሠራተኞቹ ውስጥ ኢትዮጵያውያን በጣም ጥቂት ናቸው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፣ ኢትዮጵያውያንን ማሳተፍ ላይ በትኩረት እንዲሠራም ጠይቀዋል።
ሁዋዌ የቴክኖሎጂ ግሩፕ በዓለም ላይ ከ197 ሺህ በላይ ሠራተኞች ያሉት መሆኑን ከኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
አፍሪካ ውስጥ ካሉት 8 ሺህ 600 ሠራተኞች ውስጥ 76 ከመቶ አፍሪካውያን ሲሆኑ ኢትዮጵያውያ ውስጥ ካሉ በመቶዎች ከሚቆጠሩ ሠራተኞች ውስጥ 80 ከመቶዎቹ የሀገር ውስጥ ሠራተኞች ናቸው።
I Support Ethiopia's International Internet Governance Conference - Huawei Technology Group
**********************
Huawei Technology Group announces financial and technical support for next year's International Internet Management Conference
State Minister for Innovation and Technology Huria Ali held talks with Huawei Technology Group Deputy Chief Executive Charles Ding on various issues.
He said the company would like to work with the public and private sectors in the field of information and communication technology.
State Minister for Innovation and Technology thanked Huri Ali Huawei for his support of the event.
The state minister said Huawei Technology Group has very few employees in the world and called on the state to focus on involving Ethiopians.
According to the Ministry of Innovation and Technology, Huawei Technology Group has more than 197,000 employees worldwide.
Of the 8,600 workers in Africa, 76 percent are Africans and 80 percent of Ethiopians are domestic workers.
我支持埃塞俄比亚国际互联网治理大会 - 华为技术集团
**********************
华为技术集团宣布为明年国际互联网管理大会提供资金和技术支持
创新和技术部部长胡里亚阿里与华为技术集团副首席执行官丁磊就各种问题进行了会谈。
他表示,该公司希望与信息和通信技术领域的公共和私营部门合作。
华为创新科技部部长胡里亚阿里承诺支持筹备国际互联网治理大会
Members of Defend Ethiopia said that during their stay in Ethiopia, we would like to ask the embassies that disseminate false information about Ethiopia to refrain from their actions.
በአገር ቤት ቆይታችን ኢትዮጵያን በተመለከተ የተሳሳተ መረጃ የሚያሰራጩ ኤምባሲዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ጥያቄ እናቀርባለን
**********************
በአገር ቤት ቆይታችን ኢትዮጵያን በተመለከተ የተሳሳተ መረጃ የሚያሰራጩ ኤምባሲዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ጥያቄ እናቀርባለን ሲሉ የ”ዲፌንድ ኢትዮጵያ ” አባላት ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ያደረጉትን ጥሪ ተከትሎ በተለያዩ የዓለም አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች ወደ አገር ቤት እየገቡ ነው።
ወደ አገር ቤት ከገቡ የዳያስፖራ ማህበረሰብ አባላት መካከል በ12 የአውሮፓ አገራት በመንቀሳቀስ የኢትዮጵያን እውነት ለማሳወቅ የሚሰራው “ዲፌንድ ኢትዮጵያ” አባላት ይገኙበታል።
የቡድኑ አባላት እንደሚሉት፤ በአገር ቤት ቆይታቸው መቀመጫቸውን አዲስ አበባ አድርገው ኢትዮጵያን በተመለከተ የተሳሳተ መረጃ የሚያሰራጩ ኤምባሲዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ጥሪ ያቀርባሉ።
በእንግሊዝ የ”ዲፌንድ ኢትዮጵያ” ተጠሪ አቶ ዘላለም ተሰማ፤ ቡድኑ የኢትዮጵያን እውነት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ከማሳወቅ ባለፈ አንዳንድ ምዕራባዊያን በአፍሪካ አገራት ላይ ያላቸውን የተሳሳተ አካሄድ እንዲያስተካክሉ እንደሚታገል ተናግረዋል።
ቡድኑ በኢትዮጵያ የሚገኙ የአውሮፓ አገራት አምባሳደሮች ጋር ለመወያየት እየተንቀሳቀሰ መሆኑንና በዚህም ጥያቄያቸውን በአካል ለማቅረብ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
ውይይቱ የማይሳካ ከሆነ ደግሞ ኢትዮጵያን በተመለከተ የተሳሳተ መረጃ የሚያሰራጩ ኤምባሲዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ጥያቄያቸውን በጽሁፍ እንደሚያቀርቡ አብራርተዋል።
ለአሸባሪው ህወሃት ድጋፍ የሚሰጡ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡና አሸባሪ ቡድኑ ያደረሰውን ሰብዓዊና ቁሳዊ ውድመት እንዲያወግዙ እንደሚጠይቁም ጨምረው ገልጸዋል።
አሸባሪ ቡድኑ ያወደማቸውን አካባቢዎች መልሶ ለማቋቋም የሚደረገውን ጥረት እንዲደግፉም እንዲሁ።
ኢትዮጵያ እየተደረገባት ያለውን ጫና በማሸነፍ ዳግም የአፍሪካ ነጻነት ምሳሌ እንደምትሆን ያላቸውን እምነት የተናገሩት ደግሞ ሌላኛው የቡድኑ አባል አቶ ዘላለም ጌታሁን ናቸው።
በጀርመን አገር የሚኖሩት ወይዘሮ አስቴር ሮዝስታር በበኩላቸው አሸባሪው ህወሃት በስልጣን ላይ በነበረበት ወቅት ዳያስፖራው በአገሩ ጉዳይ እንዳይሳተፍ ሲሰራ መቆየቱን አንስተዋል።
አሁን ላይ ዳያስፖራው በአገሩ ጉዳይ ላይ ንቁ ተሳታፊ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።
በተመሳሳይ በአሜሪካ ቺካጎ ነዋሪ የሆኑት አቶ የሱፍ ሃሰን፤ አገር በተቸገረችበት ጊዜ መድረስ በታሪክ ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል።
በመሆኑም ዳያስፖራው በሚችለው አቅም አገሩን መደገፍ እንደሚጠበቅበት ጥሪ አቅርበዋል።
የኢፌዴሪ ቱሪዝም ሚኒስትር ደኤታ ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት በበኩላቸው ዳያስፖራው የገና በዓልን በኢትዮጵያ ለማክበር በስፋት ወደ አገር ቤት እየገባ መሆኑን ተናግረዋል።
ዳያስፖራው የኢትዮጵያን እውነት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በማሳወቅ ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልጸው፤ ይህን ይበልጥ ለማጠናከር በቅንጅት እንደሚሰራ ገልጸዋል።
We call on embassies that disseminate false information about Ethiopia during our stay at home to refrain from their actions.
**********************
Members of Defend Ethiopia said that during their stay in Ethiopia, we would like to ask the embassies that disseminate false information about Ethiopia to refrain from their actions.
Ethiopians living in different parts of the world and friends of Ethiopia are flocking home following the call of Prime Minister Dr. Abiy Ahmed.
Among the Diaspora members are members of Defend Ethiopia, which works in 12 European countries to inform Ethiopian truth.
According to team members: They call on embassies based in Addis Ababa to refrain from spreading misinformation about Ethiopia.
Zelalem Tesema, Defend Ethiopia Representative in the United Kingdom; He said the group would not only convey Ethiopia's truth to the international community, but would also fight some Westerners to correct their misconduct in Africa.
He said the group is working to hold talks with the ambassadors of European countries in Ethiopia and will work to make their request in person.
If the talks fail, he said, embassies that spread false information about Ethiopia will be asked to refrain from their actions.
He further added that those who support the terrorist TPLF should refrain from their actions and condemn the human and material damage caused by the terrorist group.
They also support the efforts of the terrorist group to rebuild the devastated areas.
Another member of the group, Zelalem Getahun, expressed hope that Ethiopia would once again be an example of African independence by overcoming pressure.
For her part, Esther Rostster, who lives in Germany, said that during the TPLF regime, the Diaspora was not involved in the affairs of the country.
Ministry of Education to build 50 modern boarding schools" - Prof. Berhanu Nega
“ትምህርት ሚኒስቴር 50 ዘመናዊ አዳሪ ትምህርትህን ቤቶችን ያስገነባል” - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
*******************
ትምህርት ሚኒስቴር በመላ ኢትዮጵያ 50 ዘመናዊ ደረጃቸውን የጠበቁ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ለማስገንባት የሚያስችል ፕሮጀክት ማዘጋጀቱን የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስታወቁ።
በትምህርት ቤቶቹ የዲዛይን ዝግጅቱ ላይም ከኢትዮጵያ አርክቴክቶች ማኀበር ጋር ውይይት እያካሄደ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢንተርኔት አማራጭ የቪዲዮ መልዕክታቸው፤ በኢትዮጵያ 48 ሺህ ትምህርት ቤቶች ቢኖሩም ደረጃቸውን የጠበቁት 0 ነጥብ 01 በመቶዎቹ ብቻ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በአጠቃላይም ስድስት ትምህርት ቤቶች ብቻ ናቸው ደረጃ አራት ላይ የሚገኙት ብለዋል።
ስለዚህም ኢትዮጵያ ደረጃቸውን የጠበቁ የአካልና የአዕምሮ ማበልጸጊያ ትምህርት ቤቶች ያስፈልጓታል፤ ለዚህም ደረጃቸውን የጠበቁ አዳዲስ ትምህርት ቤቶችን መገንባት አለብን ብለዋል።
የኢትዮጵያ አርክቴክቶች ማኀበር በበጎ ፈቃደኝነት የትምህርት ቤቶቹን የግንባታ ዲዛይን ለማዘጋጀት ፈቃደኛ መሆኑን የገለጹት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፤ በዚህ አገራዊ ፕሮጀክት ለመሳተፍ ፈቃደኝነታቸውን ላሳዩ ኢንጂነሮችም ምስጋና አቅርበዋል።
የፕሮጀክቱን አጠቃላይ ዝግጅት በተመለከተ የኢትዮጵያ አርክቴክቶች ማኀበር አመራርና አባላት ከትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ኢፕድ ዘግቧል።
"Ministry of Education to build 50 modern boarding schools" - Prof. Berhanu Nega
*******************
The Ministry of Education has prepared a project to build 50 state-of-the-art boarding schools across Ethiopia, according to the Minister of Education, Prof. Berhanu Nega.
He said discussions are underway with the Ethiopian Architects Association on the design of the schools.
Minister of Education, Prof. Berhanu Nega's online video message; He said there are 48,000 schools in Ethiopia but only 01.01 percent have met their standard.
In total, he said, only six schools are in Level Four.
Therefore, Ethiopia needs standard physical and mental enrichment schools; "We need to build new schools that are up to standard," he said.
According to Prof. Berhanu, the Ethiopian Architects Association is willing to design the construction of the schools. He also thanked the engineers who volunteered to participate in this national project.
According to the report, the leadership and members of the Ethiopian Architects Association have held discussions with the leadership of the Ministry of Education regarding the overall preparation of the project.

Prime Minister Abiy Ahmed attends a 100-day performance review forum at federal institutions in the presence of Prime Minister Abiy Ahmed.
ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት የፌደራል ተቋማት የ100 ቀናት አፈጻጸም የግምገማ መድረክ በህዳሴው ግድብ በመካሄድ ላይ ነው
********************
ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት የካቢኔ የፌደራል ተቋማት የ100 ቀናት አፈጻጸም የግምገማ መድረክ በታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በመካሄድ ላይ ነው፡፡
ላለፉት ሳምንታት የተቋማቱን አፈጻጸም በተለያየ የቁጥጥር ስርዓቶች ሲከታተል የቆየው የፕላንና ልማት ሚንስቴርም የእያንዳንዱን ሚንስቴር ተቋማት አፈጻጸምን በመድረኩ አቅርቧል፡፡
ሚንስትሯ ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) እንዳሉት ሀገሪቱ ባስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ብታልፍም ባለፉት 100 ቀናት በዋና ዋና የማክሮ ኢኮኖሚ ዘርፎች ጥሩ ውጤት ተመዝግቧል።
ባለፉት 100 ቀናት በግብርናው ዘርፍ የመኸር ምርት መሰብሰብ እና የመስኖ ዝግጅት ስራዎች ተከናውነዋል ብለዋል።
ከወጪ ንግድም በ100 ቀናት ውስጥ ከ800 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱንም የፕላንእና ልማት ሚንስትሯ ባቀረቡት ሪፓርት ገልጸዋል ።
ኢኮኖሚው በማክሮ ደረጃ ጥሩ ውጤት እንደተመዘገበት ቢገመገምም ሀገሪቱ ተገዳ በገባችበት ጦርነት ምክንያት ከፊቱ በርካታ ፈተናዎች እንደተደቀኑበት ሚንስትሯ በግምገማ መድረኩ ላይ ተናግረዋል።
በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የተጀመረው የፌደራል ተቋማትን የሚመሩት ሚንስትሮች ስብሰባ ሁልጊዜ ከሚካሄድበት የጠቅላይሚንስትር ጽ/ቤት ወጣ ብሎ ሲካሄድ ይህ ለሁለተኛ ጊዜው ነው።
ከዚህ በፊት በኮይሻ መካሄዱም የሚታወስ ነው።
Prime Minister Abiy Ahmed attends a 100-day performance review forum at federal institutions in the presence of Prime Minister Abiy Ahmed.
********************
The Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) is undergoing a 100-day review of cabinet performance in the presence of Prime Minister Abiy Ahmed.
The Ministry of Planning and Development, which has been monitoring the performance of the institutions for the past few weeks, presented the performance of each ministry.
Minister Fitsum Assefa said the country has been in a difficult situation but has achieved good results in major macroeconomic sectors over the past 100 days.
He said harvesting and irrigation activities have been carried out in the agricultural sector over the past 100 days.
According to the Minister of Planning and Development, more than $ 800 million was earned in the first 100 days of the export trade.
"Although the economy has achieved good results at the macro level, the country is facing many challenges due to the war," she said.
This is the second time that the Prime Minister's Office has been held outside the Prime Minister's Office.
It is also worth mentioning that it was previously held in Koisha.
Tuesday, January 4, 2022
ኢትዮጵያ የምትገነባው በዕውቀት ማዕከላት ውስጥ ነው!
ዛሬ የምንመርቀው ቤተ መጻሕፍት ‹አብርሆት Enlightenment› ተብሎ ተሰይሟል። አብርሆት እውነትንና ዕውቀትን መሠረት በማድረግ ከድንቁርና ቀንበር ነጻ የመውጣት ሂደት ነው። እውነትን በአመክንዮ፣ በክርክር፣ በማስረጃ፣ በምርምር፣ የመፈለግ መንገድ ነው። ዕውቀት ወደ እውነት ለመድረስ ሁነኛው ጎዳና ነው ብሎ ያስባል። በአመክንዮ የሚመሠረት የሰው ልጆች ማኅበራዊ ኑሮ በወንድማማችነት ላይ የተመሠረተ፣ መቻቻል ያለበት፣ ነጻነትን የሚያጎላና ለለውጥ ልብን ክፍት ያደረገ እንደሆነ ያምናል፡፡ ስለዚህ የሰው ልጅ ስለራሱ፣ ስለዓለምና ስለሌላውም ሁሉ የተሻለ ዕውቀት እንዲኖረው እና ማኅበራዊ ሕይወቱን በአምክንዮ እንዲመራ ይተጋል።
ሰዎች በተመራመሩ፣ በተማሩና ባወቁ ቁጥር የተሻለ መቀራረብ ይፈጥራሉ ተብሎ ይታመናል። ድንቁርና ጨለማ ነው። በጨለማ ውስጥ ደግሞ ማወቅም መተዋወቅም አይኖርም። የሌለው ነገር ያለ፤ ያለውም ነገር የሌለ መስሎ ይታያል። የማናውቀውን ነገር እንፈራዋለን፤ እንጠላዋለንም። ስለማናውቀው ነገር የምንፈጥረው ሥዕል የተሳሳተ ነው። ለዚህ መድኃኒቱ ደግሞ ማወቅ ነው። ማወቅ መተዋወቅን ያመጣል። የምናውቀውን ነገር እንቀርበዋለን። እናምነዋለን፤ እንዛመደዋለን፤ እንወደዋለን፤ አብረነው ለመኖር ፈቃደኞች እንሆናለን።
የለውጡ ጉዞ ከተጀመረ ጊዜ አንሥቶ ከታሰበባቸው ነገሮች አንዱ ዕውቀት መር የሆነ ማኅበረሰብ መመሥረት ነው። ማኅበረሰቡ ዕውቀትን ባገኘ ቁጥር ይበልጥ ይተዋወቃል፤ ይቀራረባል፤ ይተማመናል። አንዱ ስለሌላው የያዘውን የተሳሳተ ግምት በመተው በትክክለኛው ዕውቀት ላይ የተመሠረተ መረዳትን ይይዛል። ለዚህ ደግሞ የትምህርት ተቋማትን ሪፎርም ማድረግ፤ ነባር ዕውቀቶችን ለሀገራዊ ልማት መጠቀም፤ ምርምሮችንና ጥናቶችን፤ ውይይቶችንና ክርክሮችን፤ ነጻ ሐሳብ መድረኮችን፤ ኪነ ጥበብን ማበረታታት፤ ደራስያንና የሐሳብ መሪዎችን ወደፊት ማምጣት፤ የለውጡ አንዱ መንገድ ሆኖ ቆይቷል።
በለውጡ ዘመን አርአያ ሆነው የተሠሩትን ሥራዎች ስናይ ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው በተጨማሪ የአብርሆት ጠቀሜታቸው የጎላ ነው። የአንድነት ፓርክና የአድዋ ሙዝየም ታሪክን ለመጣያና ለመለያያ ሳይሆን ለመተዋወቂያና መተራረሚያ ለማድረግ የቆመ ነው። የመስቀል አደባባይ እድሳትና የሸገር ፓርክ ግንባታ ሃይማኖት፣ ባህልና ኪነ ጥበብ ለሚያመጡት አብርሆት በር የከፈተ ነው። የእንጦጦ የሥዕል ጋለሪ አብርሆትን ከሚያስገኙት ረቂቅ ጥበቦች ለሁለቱ ለሙዚቃና ሥዕል ዕድል የሰጠ ነው። መዝናኛ የሚመስሉት የእንጦጦ ፓርክ፣ የቸርቸር ጎዳናና ወንዝ ዳር ፕሮጀክቶች አእምሮን ከተዋጊነትና ከግጭት አምራችነት ለማስፈታትና የሰከነ የሐሳብ መድረክን እንዲመርጥ ለማድረግ ታስበው የተሠሩ ናቸው። የጎርጎራ፣ የወንጪና የጨበራ ጩርጩራ ፕሮጀክቶች ለአንድ ዓላማ በሕዝቦች መካከል መገናኘትን፣ መተዋወቅን እና መደናነቅን ለመፍጠር ነው። የመለያየትን ግንብ አፍሮ የኅብረ ብሔራዊ አንድነትን መስክ ለመፍጠር ነው።
ኢትዮጵያ የራሳቸውን ፊደል ቀርጸው፣ የራሳቸውን ትምህርት አደራጅተው፣ የራሳቸውን ታሪክ ከጻፉ ጥቂት የዓለም ሀገሮች አንዷ ናት። በእስልምናና ክርስትና ማዕከላት ብቻ ከ250ሺ በላይ በእጅ የተጻፉ መጻሕፍት በየገዳማቱና በየመስጊዶቹ ያሏት ሀገር ናት። በአፍሪካ የመጀመሪያውን ልቦለድ የጻፈች ሀገር ናት። ልጆቿ ዕውቀትን ፍለጋ ከቦታ ቦታ ሲዘዋወሩ፤ ሀገር አቋርጠውም ሲንከራተቱ የኖሩባት ሀገር ናት። ምንም እንኳን ሺ ዘመናትን የተሻገረ የሥነ ጽሑፍ ሥራና የትምህርት ተቋም ቢኖራትም፤ በመቶ ሺዎች የሚጠጉ መጻሕፍትን ብታመርትም፤ ዕውቀትን በማዕከል ይዘው ለዕውቀት ፈላጊዎች ተደራሽ የሚያደርጉ ማዕከላት ግን በብዛትና በብቃት የሏትም።
እስካሁን ከዩኒቨርሲቲዎች ውጭ ያለን ትልቁ ቤተ መጻሕፍት አንድ ነው። እርሱም በ1936 ዓም የዛሬ 78 ዓመት የተከፈተው ብሔራዊ ቤተ መጻሕፍትና ቤተ መዛግብት ነው። እንደ እውነቱ ከሆነ እስከ ዛሬ ድረስ ቢያንስ በዞን ደረጃ አንድ ትልቅ ቤተ መጻሕፍት ሊኖረን ይገባ ነበር። ግን አልሆነም። ይህ አብርሆት ቤተ መጻሕፍት ሲታሰብ አምስት አገልግሎቶችን እንዲያካትት ሆኖ ነው። በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ የተጻፉ መጻሕፍት እንዲገኙበት። አካል ጉዳተኞችን ጨምሮ የተሻለ የማንበቢያ ሥፍራ እንዲኖረው። ዲጂታል አገልግሎት መስጠት እንዲችል። በቂ የሆነ የመኪና ማቆሚያ እንዲኖረውና በአካባቢው ያለውን የመናፈሻ ሥፍራ ለመጠቀም በሚያስችል ሁኔታ አገልግሎት እንዲሰጥ።
ከሥነ ሕንጻው ጀምሮ ዕውቀትንና ታሪክን እንዲያንጸባርቅ ተደርጎ የተገነባ ነው። ‹አብርሆት ቤተ መጻሕፍት› የተባለውም ዋና ዓላማው እውነትና ዕውቀት ነጻ የሚያወጣውን ማኅበረሰብ ለመመሥረት ስለሆነ ነው። ኢትዮጵያ ለልጆቿ የሥልጣኔን መንገድ መርጣለች። ለጠላቶቿ ደግሞ ክንደ ብርቱ ሆና ትጠብቃቸዋለች። የሥልጣኔው መንገድ ደግሞ መማር፣ መመራመር፣ መወያየት፣ መከራከር፣ በሐሳብ መሸናነፍ፣ ዕውቀትን ማነፍነፍ፣ በአመክንዮ፣ በማስረጃና በመረጃ ላይ መመሥረት ናቸው። በቀጣዩ ዘመን፣ መጀመሪያ ደረጃቸውን የጠበቁ ክልላዊ አብያተ መጻሕፍት እንዲኖሩን፤ በመቀጠልም ዞናዊና ወረዳዊ አብያተ መጻሕፍት እንዲኖሩን እንሠራለን። ኢትዮጵያ የምትገነባው በየደረጃው በሚደራጁ የዕውቀት ማዕከላት ውስጥ ነው።
ለዚህ ደግሞ ባለ አራት ማዕዘን ኅብረት ያስፈልገናል። መንግሥት፣ የአካባቢው ሕዝብ፣ በጎ አድራጊ አካላትና በውጭ የሚኖረው ኢትዮጵያዊ። መንግሥት ቦታዎችን ያመቻቻል፤ አስተዳደሩን ይወስዳል። የአካባቢው ማኅበረሰብ የዐቅሙን አዋጥቶ ግንባታውን ያግዛል። በጎ አድራጊዎችም በግንባታው ላይ ይሳተፋሉ። በውጭ የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ደግሞ መጻሕፍቱን በማሰባሰብ፣ በቴክኖሎጂ የተሟላ እንዲሆን በማድረግና ዘመናዊ አሠራር በመዘርጋት አስተዋጽዖ ያደርጋል። እንደዚህ ከሆነ ዕውቀት እንደ ኢትዮጵያ ጅረቶች በየአካባቢው ይፈስሳል፤ ትውልድንም ያጠጣል። የነገዋ ኢትዮጵያ ከዛሬ በእጅጉ የተሻለች ትሆናለች፤ መሠረቷን እውቀት ያደረገች ሥልጡን ሀገር ትሆናለች።
ይህ ቤተ መጻሕፍት ሲታሰብ፣ ሲገነባና ሲሟላ አስተዋጽዖ ያደረጉትን ሁሉ በዚሁ አጋጣሚ ላመሰግን እወዳለሁ። ሕዝቡ ቤተ መጻሕፍቱን ተንከባክቦ፣ እንዳይበላሽ ጠብቆ፤ ሲጎዳ ጠግኖ፤ ሲጎድል አሟልቶ ለልጅ ልጅ በሚተርፍ መንገድ እንዲጠቀምበት አደራ እላለሁ።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ታህሳስ 22፣ 2014 ዓ.ም
ደቡብ አፍሪካውያን ወጣቶች ኢትዮጵያ የምታደርገውን ትግል በሁሉም መስክ ይደግፋሉ፦ ላታታ ላክስ
ደቡብ አፍሪካውያን ወጣቶች ኢትዮጵያ የምታደርገውን ትግል በሁሉም መስክ ይደግፋሉ፦ ላታታ ላክስ
**********************
ወደ ኢትዮጵያ የመጣው የደቡብ አፍሪካው የማህበረሰብ መሪ ላታታ ላክስ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ እና ከፐብሊክ ዲኘሎማሲ ቡድን ተወካዮች ጋር ተወያይቷል።
በውይይታቸውም አምባሳደር ዲና የኢትዮጵያን ድምፅ ለማሰማት እና ለመደገፍ ላክስ እያደረገ ላለው ጥረት ምስጋና አቅርበዋል።
ወጣቱ ላክስ የውጭ ሃይሎች በኢትዮጵያ ላይ የሚከተሉትን ጣልቃ ገብነት በተደጋጋሚ ሲያወግዝ የነበረ ሲሆን ደቡብ አፍሪካ ላይ በነበረው የበቃ #nomore እንቅስቃሴም ሰፊ ተሳትፎ ሲያደርግ ቆይቷል።
ወጣቱ ደቡብ አፍሪካዊ ላክስ በበኩሉ የነፃነት ምልክት በሆነችው ኢትዮጵያ መገኘቱ ልዩ ደስታ እንደፈጠረበት ተናግሯል።
ኢትዮጵያ የገጠማትን ፈተና በሁሉም መስክ እንድትወጣ ወጣቶች መሪ ሃላፊነት መወጣት እንዳለባቸው ተናግሯል።
እርሱ እና ሌሎች ደቡብ አፍሪካውያን ወጣቶች ኢትዮጵያውያን የሚያደርጉትን ትግል በሁሉም መስክ እንደሚደግፍ ላታታ ላክስ ገልጿል።
ላክስ በሚኖርበት አካባቢ የሶዌቶ ማህበረሰብን በማደራጀት በሚያደርጋቸው ንቅናቄዎች ከፍተኛ ተፅዕኖ እያሳደረ የሚገኝ ወጣት ነው።
The Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) has successfully completed preparations to launch a power plant test in the coming days.
Congratulations‼ ️‼ ️ Congratulations 🙏
ER The Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) has successfully completed preparations to launch a power plant test in the coming days.
Capacity reports that experimental power generation on the dam has been completed.
"Ethiopia is preparing to generate pre-emptive power for its major national flagship project," Bekele said. Within a maximum of 5 weeks, our dam will start generating power !!!!
Our dam is expected to generate 700MW of pre-generating power !! Currently, the overall construction of the dam has reached 82 percent
What could be more exciting news than victory?!?
The time has come for the situation of our country to change.
👉 Congratulations again !! Congratulations ️ ️ CONGRATULATIONS 🎉🎊
Dejen expanded
እንኳን ደስ አለን‼️ ‼️ እንኳን ደስ አላችሁ🙏
📌 ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ GERD የኃይል ማመንጫ ሙከራውን በመጪዎቹ ቀናት ውስጥ ለመጀመር ዝግጅቱን በተሳካ ሁኔታ አጠናቋል።
በግድቡ ላይ የሙከራ ሃይል የማመንጨት ስራው መጠናቀቁን ካፒታል ዘግቧል።
ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ በቀለ "ኢትዮጵያ በታላቁ ብሄራዊ ፍላግሽፕ ፕሮጀክቷ ቅድመ ሃይል ለማመንጨት በዝግጅት ላይ ትገኛለች" ብለዋል። ቢበዛ በ5 ሳምንት ጊዜ ውስጥ ግድባችን ኃይል ማመንጨት ይጀምራል!!!!
ግድባችን በቅድመ-ኃይል ማመንጫው 700MW ያመነጫል ተብሎ ይጠበቃል!! አሁን ላይ የግድቡ አጠቃላይ የግንባታ ሂደትም 82 በመቶ ደርሷል።🙏️
ከዚህ በላይ ምን የሚያስደስት የድል ዜና ይኖራል?!?
የሃገራችን ሁኔታ የሚቀየርበት ጊዜው ቀርቧል።
👉በድጋሚ እንኳን ደስ አለን!! እንኳን ደስ አላችሁ‼️ CONGRATULATIONS 🎉🎊
Felicitaciones‼ ️‼ ️ Felicitaciones 🙏
ER La Gran Presa del Renacimiento Etíope (GERD) ha completado con éxito los preparativos para lanzar una prueba de planta de energía en los próximos días.
Capacity informa que se ha completado la generación de energía experimental en la presa.
"Etiopía se está preparando para generar poder preventivo para su principal proyecto insignia nacional", dijo Bekele. ¡En un máximo de 5 semanas, nuestra presa comenzará a generar energía!
¡Se espera que nuestra presa genere 700MW de energía pregeneradora! Actualmente, la construcción general de la presa ha alcanzado el 82 por ciento.
¿Qué podría ser una noticia más emocionante que la victoria?
Ha llegado el momento de que cambie la situación de nuestro país.
👉 ¡¡Felicidades de nuevo !! Felicitaciones ️ ️ FELICIDADES 🎉🎊
Expansor dejen
.ለጠላት የእሳት ነበልባል የሆኑት አባት እና ልጅ
ለጠላት የእሳት ነበልባል የሆኑት አባት እና ልጅ
አቶ ጋሻዉ ሹምዬ ይባላሉ፤ በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ወረዳ የድብ ባሕር ቀበሌ ነዋሪ እና የስምንት ልጆች አባት ናቸዉ። አብሮ ዘማች የበኩር ልጃቸው ደግሞ ደረጀ ጋሻው ይባላል፡፡ አባት እና ልጅ ሀገር ለማፍረስ ወደ አካባቢያቸው የመጣዉን አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን በምን መልኩ መደምሰስ እና መቀበሪያውን እዚያዉ ማድረግ እንደሚችሉ ተማከሩ፤ አደረጉትም። አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን ነሐሴ እና ጳጉሜን ወራት በአካባቢያቸው የፈጸመውን ወረራ ለመመከት ከወገን ጦር ጋር አብረው ተፋልመዋል፡፡
አባት እና ልጅ በወገን ጦር በደረሰበት ከባድ ምት የተፍረከረከውን አሸባሪ የትግራይ ወራሪ ቡድን እየተከታተሉ በመልቀም እና ዋሻ ውስጥ ተቆርጠዉ የቀሩትን የቡድኑን አባላት በመፋለም ሦስቱን አቁስለዉ አምስቱን ማርከዉ በአጠቃላይ ስምንቱን ለመከላከያ ሠራዊት አስረክበዋል፡፡
ጀግናው አቶ ጋሻዉ “አባቴ አርበኛ ነዉ፤ የአባቴን መሳሪያ ይዤ ነዉ የዘመትኩት፤ የእርሱ ልጅ በመሆኔ ኩራት ይሰማኛል፤ ይህም ጠንክሬ ሀገሬን ከአሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን እንድታደግ አድርጎኛል” ነው ያሉን፡፡ ጀግናው አቶ ጋሻው አሁንም ስሜታቸዉ እንደጋለ፤ ደማቸዉ እንደሞቀ ነዉ፤ ሀገራቸውን ለማፍረስ የመጣውን ጠላት ደምስሰውታል።
የበኩር ልጃቸዉ ደረጀ ጋሻዉ በሰኔ ወር 2013 ዓ.ም ከቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋም ነበር የተመረቀዉ፤ ገና ሥራ ይዞ አዲስ ሕይወት ሳይጀምር ነበር ሀገር አፈርሳለሁ ብሎ የመጣን አሸባሪ የትግራይ ወራሪ ቡድን ለመደምሰስ ሀገራዊ ጥሪዉን ተቀብሎ ከአባቱ ጋር የዘመተዉ።
“ሀገራችን ወረራ ሲፈፀምባት ቆሞ የሚያይ በዝምታ የሚያልፍ ወጣት የለም፤ እኔም እስከመጨረሻዉ ጠላቷን ልደመስስላት ነዉ ወደ ትግሉ የተቀላቀልኩት” ያለዉ ወጣት ደረጀ እጁ ላይ የተወሰነ ጉዳት ደርሶበት ሕክምና አድርጎ ወደ ግንባር መዝመቱን ተናግሯል።
“ታላቅ ሀገር ለሆነችው ኢትዮጵያ የሚከፈልላት ዋጋ ከመቁሰልም በላይ ነዉ” ሲል ነው ወጣቱ የገለጸው፡፡
“የአባቶቻችን ልጆች በመሆናችን እጅጉን ልንኮራ ይገባል፤ ሁላችንም የእነርሱን የጀግንነት ታሪክ በመድገም አሻራችንን እናሳርፍ” ብሏል።
ዛሬም አዳዲስ ጀግኖች ተፈጥረዋል፤ እኛም የሠሩትን ገድል መግለጣችንን እንቀጥላለን።
Ethiopia is the second country for all Africans," said Senegal's ambassador
"ኢትዮጵያ ለመላው አፍሪካውያን ሁለተኛ ሀገር ናት" ፦የሴኔጋል አምባሳደር
*******************
ኢትዮጵያ ለመላው አፍሪካውያን ሁለተኛ ሀገር ናት ሲሉ በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙት የሴኔጋል አምባሳደር መሀመድ ላሚን ቲያው ገለጹ።
አምባሳደሩ የሹመት ደብዳቤያቸውን ቅጂ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኘሮቶኮል ጉዳዮች ምክትል ሹም ለሆኑት አምባሳደር ዓለማየሁ ሰውአገኝ አቅርበዋል።
በወቅቱም ተሿሚ አምባሳደሩ ኢትዮጵያ ለመላው አፍሪካ ሁለተኛ ሀገር መሆኗን ጠቅሰው ÷ ሴኔጋል ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ታሪካዊ የሁለትዮሽ ግንኙነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ፍላጎት መኖሩን ተናግረዋል።
በሥራ ቆይታቸውም በሁለቱ ሀገራት መካከል በባሕል እና ቱሪዝም ዘርፎች ያለውን ትብብር ለማስፋት እና በኢንዱስትሪ ፓርክ ዘርፍ ከኢትዮጵያ ልምድ ለመቅሰም እንደሚፈልጉም ጠቁመዋል።
አምባሳደር ዓለማየሁ በበኩላቸው ÷ ሴኔጋልና ኢትዮጵያ ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን አንስተው ÷ የሁለቱ ሀገራት ህዝቦችም ይበልጥ ተጠቃሚ በሚያደርጉ መስኮች ላይ አተኩረው መሥራት እንደሚገባቸው ገልጸዋል።
አምባሳደሩ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው የሥራ ቆይታ የተሳካ ስራ ማከናወን እንዲችሉ ተገቢው ትብብር እንደሚደርግላቸውም አምባሳደር ዓለማየሁ እንዳረጋገጡላቸው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
"Ethiopia is the second country for all Africans," said Senegal's ambassador
*******************
New Ethiopian Ambassador to Ethiopia Mohamed Lamin Tiaw
The Ambassador presented a copy of his credentials to Ambassador Alemayehu Seguegen, Deputy Chief of Protocol at the Ministry of Foreign Affairs.
He said Ethiopia is the second largest country in Africa and that Senegal wants to strengthen its historic bilateral relations with Ethiopia.
He said the two countries would like to expand cooperation between the two countries in the fields of culture and tourism and gain experience in the industrial park sector.
Ambassador Alemayehu on his part said Senegal and Ethiopia have strong diplomatic relations and the people of the two countries should focus on areas that benefit them the most.
Subscribe to:
Posts (Atom)
Curated Products for Generation X
https://amzn.to/3VhbwJz GenX Essentials - Curated Products for Generation X ...
-
አሁን ስንት ሰአት ነው?
-
Ghost Town (1) Les Miserables (5) Pet Sematary (3)&"Handmade" (22)"SRT" by North End (1)"Yes (1)"Yes...
-
Guide to Starting a Small-Scale Tissue & Napkin Business Step 1: Acquire Equipment & Machinery Plan on key converting machines a...
Recomanded Web sites
Do you need Ethiopian Power of Attorney where your agent can preform several crucial tasks on your behalf? Such as adoption proceedings, buying movable or immovable properties, paying tax, represent you in governmental and public offices and several others tasks with our your physical presence? If your answer is yes get the Ethiopian Power of Attorney or YEBBO now on sale